- Details
ቀጠናዊ የኢንዱስትሪ ትስስር ፎረሙ ከአከባቢው ኢንዱስትሪዎችና ቴክ/ሙ/ትም/ሥ/ኮሌጆች በዳሰሳ ጥናት የተገኙ ውጤቶች፣ የ2014 ዕቅድ አፈፃፀምና የ2015 ዓ.ም ዕቅድ ዙሪያ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ጥቅምት 26/2/2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ተወያይቷል፡፡ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ቀጠናዊ የእንዱስትሪ ትስስር ፎረም ጉባዔ በአርባ ምንጭ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ተካሄደ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ2014 ዓ/ም ምሩቃን በብቃት መመዘኛ ፈተና አበረታች ውጤት ማስመዝገባቸው ተገልጿል፡፡ የብቃት መመዘኛ ፈተናው በፌዴራል ጤና ሚኒስቴርና በከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ በየዓመቱ የሚሰጥ ነው፡፡
Read more: የ2014 ዓ/ም በሕክምናና ጤና ሳይንስ ምሩቃን በብቃት መመዘኛ ፈተና አበረታች ውጤት ማስመዝገባቸው ተገለጸ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በሒሳብ ትምህርት ከፍል በ‹‹Opበአርባ ምንጭ ዩኒቨርeration Research›› ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩት ዕጩ ዶ/ር ሀብታሙ ፀጋዬ የምርምር ሥራቸውን ኅዳር 3/2015 ዓ/ም የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርበው ተገምግሟል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተርነት ውድድር ነሐሴ 19/2014 ዓ.ም በወጣው ማስታወቃያ መሠረት የቀረቡ 7 ዕጩ ተወዳዳሪዎች የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ አባልና የኢትዮጵያ ሚትዮሮሎጂ ኤጀንሲ ዳይሬክተር፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንትና ም/ፕሬዝደንቶች፣ የሴኔት አባላት፣ የመምህራን ማኅበር ተወካይ፣ የተማሪ ኅብረት ተወካይና የአስተዳዳር ሠራተኞች ተወካይ በተገኙበት የስትራቴጂክ ዕቅዶቻቸውን ኅዳር 6/2015 ዓ.ም ካቀረቡ በኋላ የሴኔት ድምጽ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት ተከናውኗል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ለፊዚክስ ትምህርት ክፍል ቤተ-ሙከራ በተገዙ ቁሳቁሶች አጠቃቀም ዙሪያ የአሠልጣኞች ሥልጠና ከጥቅምት 28 -ኅዳር 11/2015 ዓ/ም ለተከታታይ 15 ቀናት እየተሰጠ ይገኛል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ለፊዚክስ ቤተ-ሙከራ አዲስ በተገዙ ቁሳቁሶች አጠቃቀም ዙሪያ ሥልጠና እየተሰጠ ነው