ቀጠናዊ የኢንዱስትሪ ትስስር ፎረሙ ከአከባቢው ኢንዱስትሪዎችና ቴክ/ሙ/ትም/ሥ/ኮሌጆች በዳሰሳ ጥናት የተገኙ ውጤቶች፣ የ2014 ዕቅድ አፈፃፀምና የ2015 ዓ.ም ዕቅድ ዙሪያ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ጥቅምት 26/2/2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ተወያይቷል፡፡ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ2014 ዓ/ም ምሩቃን በብቃት መመዘኛ ፈተና አበረታች ውጤት ማስመዝገባቸው ተገልጿል፡፡ የብቃት መመዘኛ ፈተናው በፌዴራል ጤና ሚኒስቴርና በከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ በየዓመቱ የሚሰጥ ነው፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በሒሳብ ትምህርት ከፍል በ‹‹Opበአርባ ምንጭ ዩኒቨርeration Research›› ትምህርት ፕሮግራም  የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩት ዕጩ ዶ/ር ሀብታሙ ፀጋዬ የምርምር ሥራቸውን ኅዳር 3/2015 ዓ/ም የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርበው ተገምግሟል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተርነት ውድድር ነሐሴ 19/2014 ዓ.ም በወጣው ማስታወቃያ መሠረት የቀረቡ 7 ዕጩ ተወዳዳሪዎች የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ አባልና የኢትዮጵያ ሚትዮሮሎጂ ኤጀንሲ ዳይሬክተር፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንትና ም/ፕሬዝደንቶች፣ የሴኔት አባላት፣ የመምህራን ማኅበር ተወካይ፣ የተማሪ ኅብረት ተወካይና የአስተዳዳር ሠራተኞች ተወካይ በተገኙበት  የስትራቴጂክ ዕቅዶቻቸውን  ኅዳር 6/2015 ዓ.ም ካቀረቡ በኋላ የሴኔት ድምጽ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት ተከናውኗል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ለፊዚክስ ትምህርት ክፍል ቤተ-ሙከራ በተገዙ ቁሳቁሶች አጠቃቀም ዙሪያ የአሠልጣኞች ሥልጠና ከጥቅምት 28 -ኅዳር 11/2015 ዓ/ም ለተከታታይ 15 ቀናት እየተሰጠ ይገኛል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ