- Details
ዓለም አቀፍ የነጭ ሪባን ቀን “ሴቷን አከብራለሁ! ጥቃቷንም እከላከላለሁ!” በሚል መሪ ቃል ከሳውላን ካምፓስ ውጪ ባሉ በዩኒቨርሲቲው 5 ካምፓሶች ኅዳር 19/2015 ዓ/ም በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡ በዓሉም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለ31ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ17ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሲዊዘርላንድ ሀገር ከሚገኝ "Eawag" ከተሰኘ የምርምር ማዕከል ጋር በመሆን ለውሃ አቅርቦትና አካባቢ ምኅንድስና ፋከልቲ መምህራን በሳኒቴሽን ዘዴና ቴክኖሎጂ ምርጫ /Sanitation System and Technology Choices/ በሚል ርዕስ ከኅዳር 15-16/2014 ዓ.ም ድረስ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልጸጊያ ማዕከል አዘጋጅነት በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለ9ኛ ጊዜ የሚከበረው የሥራ ዕድል ፈጠራ ሳምንት በዩኒቨርሲቲው ለመጀመሪያ ጊዜ ኅዳር 16/2015 ዓ/ም በፓናል ውይይትና የቢዝነስ ውድድር በማካሄድ በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የዓለም የሥራ ዕድል ፈጠራ ሳምንት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክቶሬት የ2015 ዓ/ም የቴክኖሎጂ ሽግግር ንድፈ ሃሳቦችን መምህራን፣ ተመራማሪዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች በተገኙበት ኅዳር 13/2015 ዓ/ም አስገምግሟል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክቶሬት የቴክኖሎጂ ሽግግር ንድፈ ሃሳቦች ግምገማ አካሄደ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ ጉድኝት ማስ/ጽ/ቤት ከጋሞ ዞን ገቢዎች ባለሥልጣንና ከካምባ ከተማ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በካምባ ከተማ ለሚገኙ ነጋዴዎችና ግብር ሰብሳቢ ባለሙያዎች በሂሳብ መዝገብ አያያዝ ዙሪያ ከኅዳር 8-9/2015 ዓ/ም ድረስ የ2 ቀናት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡