ዓለም አቀፍ የነጭ ሪባን ቀን “ሴቷን አከብራለሁ! ጥቃቷንም እከላከላለሁ!”  በሚል መሪ ቃል ከሳውላን ካምፓስ ውጪ ባሉ በዩኒቨርሲቲው 5 ካምፓሶች ኅዳር 19/2015 ዓ/ም በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል፡፡ በዓሉም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለ31 ጊዜ በሀገራችን ለ17 ጊዜ እየተከበረ ይገኛል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሲዊዘርላንድ ሀገር ከሚገኝ "Eawag" ከተሰኘ የምርምር ማዕከል ጋር በመሆን ለውሃ አቅርቦትና አካባቢ ምኅንድስና ፋከልቲ መምህራን በሳኒቴሽን ዘዴና ቴክኖሎጂ ምርጫ /Sanitation System and Technology Choices/ በሚል ርዕስ ከኅዳር 15-16/2014 ዓ.ም ድረስ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልጸጊያ ማዕከል አዘጋጅነት በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለ9 ጊዜ የሚከበረው የሥራ ዕድል ፈጠራ ሳምንት በዩኒቨርሲቲው ለመጀመሪያ ጊዜ ኅዳር 16/2015 ዓ/ም በፓናል ውይይትና የቢዝነስ ውድድር በማካሄድ በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክቶሬት የ2015 ዓ/ም የቴክኖሎጂ ሽግግር ንድፈ ሃሳቦችን መምህራን፣ ተመራማሪዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች በተገኙበት ኅዳር 13/2015 ዓ/ም አስገምግሟል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡ 

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ ጉድኝት ማስ/ጽ/ቤት ከጋሞ ዞን ገቢዎች ባለሥልጣንና ከካምባ ከተማ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በካምባ ከተማ ለሚገኙ ነጋዴዎችና ግብር ሰብሳቢ ባለሙያዎች በሂሳብ መዝገብ አያያዝ ዙሪያ ከኅዳር 8-9/2015 ዓ/ም ድረስ የ2 ቀናት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡