- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለ7ኛ ዙር ያሠለጠናቸውን 87 የሕክምና ዶክተሮችን በመጪው ቅዳሜ ታኅሣሥ 24/2013 ዓ/ም በድምቀት ያስመርቃል፡፡ ከተማራቂዎቹ መካከል 32ቱ ሴቶች ሲሆኑ 55ቱ ወንዶች ናቸው፡፡
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 87 የሕክምና ዶክተሮችን በመጪው ቅዳሜ ያስመርቃል
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከIBRO እና DANA ፋውንዴሽኖች ጋር በመተባበር የአንጎል ግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንትን ምክንያት በማድረግ ለኮሌጁ መምህራን፣ ተመራማሪዎችና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች እንዲሁም ለመሰናዶ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ከታኅሣሥ 12-16/2013 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ የአዕምሮ ጤና ምንነት፣ የአዕምሮ ጤና እድገት እና የአዕምሮ ጤናን የሚጎዱ ሱሶችና አደንዛዥ ዕጾች የሥልጠናው ይዘቶች ናቸው፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
የጤና ሚኒስቴር ልዑካን ቡድን ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና ከጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ባለድርሻ አካላት ጋር የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ አፈፃፀምን ታኅሣሥ 16/2013 ዓ/ም ጎብኝቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የጤና ሚኒስቴር ልዑካን ቡድን የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ አፈፃፀምን ጎበኘ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከኢትዮጵያ ሕክምና ማኅበር ጋር በመተባበር ‹‹ጠንካራ እና ታማኝ ሐኪም ለተሻለ ጤና!›› በሚል መሪ ቃል በኮሌጁ ሥር ለሚገኙ የሕክምና ባለሙያዎች ታኅሣሥ 17/2013 ዓ/ም በሙያ ማሻሻያ ዙሪያ ሥልጠና የሰጠ ሲሆን የጋራ መግባቢያ ሰነድም ተፈራርሟል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለሕክምና ባለሙያዎች በሙያ ማሻሻያ ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንትነት እና ለምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንትነት ኅዳር 21/2013 ዓ/ም ባወጣው ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ መሠረት የውድድሩ አካል የሆነው ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ገለጻ ታኅሣሥ 7/2013 ዓ/ም ለሴኔቱ ቀርቧል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝደንትነት ውድድር ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ገለጻ ቀረበ