- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፌዴራል የፍትሕ እና የሕግ ምርምርና ሥልጠና ኢንስቲትዩት እና ከኢትዮጵያ የሕግ ት/ቤቶች ማኅበር ጋር በመተባበር ‹‹Contemporary Challenges, Trends and Governance of Internally Displaced Persons Protection in Ethiopia›› በሚል ርዕስ 2ኛውን ዓመታዊ የምርምር ጉባዔ አካሂዷል፡፡ በጉባዔው ከተለያዩ የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት በመጡ ምሁራን ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ት/ቤት 2ኛውን ዓመታዊ የምርምር ጉባዔ አካሄደ
- Details
የሕግ ት/ቤት በሽግግር ፍትሕ አማራጮች ያለፉ ጉዳዮች መፍታት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ የዩኒቨርሲቲው ሕግ ተማሪዎች፣ መምህራንና ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ የተወጣጡ ግለሰቦች በተገኙበት ታኅሣሥ 12/2014 ዓ/ም ሴሚናር አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር 28ኛው ሀገር አቀፍ ኮንፍራንስ ላይ ከቀረቡ ሳይንሳዊ የምርምር ውጤቶች ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቅ ሀና እንዳሻውና በማስተርስ ዲግሪ ምሩቅ ሁሴን አሊ የላቀ የመመረቂያ ጽሑፍ በማቅረብ ታኅሣሥ 9/2014 ዓ/ም ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
Read more: በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር ኮንፍራንስ 2 የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ምሩቃን በላቀ የመመረቂያ ጽሑፍ ተሸላሚ ሆኑ
- Details
በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የኤሌትሪካል እና ኮምፕዩተር ምኅንድስና ፋከልቲ መምህር፣ ተመራማሪና አማካሪ የሆኑት ዶ/ር አንቺት ቢጀልዋን (Dr Anchit Bijalwan) ‹‹Network Forensics፡ Privacy and Security›› በሚል ርዕስ 2ኛ መጽሐፋቸውን አሳትመዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: ዶ/ር አንቺት ቢጀልዋን ‹‹Network Forensics፡ Privacy and Security›› በሚል ርዕስ 2ኛ መጽሐፋቸውን አሳተሙ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ የ2013 ዓ/ም የሥራ አፈጻጸምን መሠረት በማድረግ በመማር ማስተማር፣ በጥናትና ምርምር፣ በማኅበረሰብ አገልግሎት እንዲሁም በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ከዩኒቨርሲቲው መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችና የካውንስል አባላት ጋር ከታኅሣሥ 7-9/2014 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ከዩኒቨርሲቲው መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችና የካውንስል አባላት ጋር ውይይት አካሄደ