የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የልማት ሥራዎች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በተለያዩ ወረዳዎች እየተሠሩ ያሉ የአካባቢና ደን ጥበቃ ሥራዎች ያሉበት ነባራዊ ሁኔታና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ታኅሣሥ 25/2014 ዓ/ም ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ እየተሠሩ ያሉ የአካባቢና ደን ጥበቃ ሥራዎች፣ ያሉባቸው ችግሮችና የ2014 ዓ/ም የችግኝ ስርጭት ዕቅድ በውይይቱ ተነስተዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲው የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ማኅበረሰብ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት (ገና) በዓል በሠላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣ የአንድነትና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልጻል!!

መልካም ገና!!

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከደቡብ ክልል ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲና ከጋሞ ዞን ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ጋር በመተባበር በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ቆላ ሻራ ቀበሌ እንዲሁም በምዕራብ ዓባያ ወረዳ አንኮበርና ኤልባ ቀበሌያት የሚገነቡትን የባዮ ጋዝ ማብለያዎች ታኅሣሥ 22/2014 ዓ/ም የመስክ ምልከታ አካሂደዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ጽ/ቤት በኮቪድ-19 ዙሪያ በተሠሩ 28 ምርምሮች ላይ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ታኅሣሥ 22/2014 ዓ.ም ግምገማዊ ወርክሾፕ አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በጥናትና ምርምር ተደግፎ ለኢትዮጵያውያን ሕጻናት፣ መምህራንና ወላጆች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ንባብ ክሂል ለመማሪያና ለማስተማሪያ የሚሆን “Easy Ways to Read in English” ወይም “የእንግሊዝኛ ቋንቋ ፍኖተ-ንባብ” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ታኅሣሥ 26/2014 ዓ/ም ከጧቱ 02፡30 ጀምሮ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት፣ የእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ት/ክፍል መምህራን፣ ተጋባዥ እንግዶች፣ የጋሞ ዞንና በዞኑ የሚገኙ ወረዳዎች የትምህርት ሴክተር ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ መግቢያ በር አካባቢ በሚገኘው አዳራሽ የውይይትና የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ይካሄዳል፡፡