ተማሪ አየለ አካሉ ከእናቱ ወ/ሮ ሙሉነሽ መርሻ እና ከአባቱ ከአቶ አካሉ ወልደኪዳን በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ ሰላ ድንጋይ ፍላገነት ቀበሌ በ1991 ዓ/ም ተወለደ፡፡ ተማሪ አየለ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በወረዳው እምቧይ ባድ ሙሉ 1 ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የ2 ደረጃ ትምህርቱን በሳሲት አጠቃላይ 2 ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም የመሰናዶ ትምህርቱን በሰላ ድንጋይ አጠቃላይ 2 ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት ተከታትሏል፡፡

ወ/ሮ ምሥራቅ ምስክር ከአባታቸው አቶ ምስክር ምንዳ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ካቡሬ ኮሎ በአርባ ምንጭ ከተማ ወዜ ቀበሌ ጥቅምት 12/1985 ዓ/ም ተወለዱ፡፡ ወ/ሮ ምሥራቅ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ ሙሉ 1 ደረጃ ት/ቤት እና የ2ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ አጠቃላይ 2 ደረጃ ት/ቤት ያጠናቀቁ ሲሆን በአርባ ምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለ3 ዓመት ሠልጥነው ጥቅምት 24/2005 ዓ/ም በፋርማሲ ቴክኒሺያንነት በደረጃ 4 ተመርቀዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ጽ/ቤት ከአግታ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ጋር በመተባበር ከጠቅላላ አገልግሎትና አውቶሞቲቭ ኢንጂነሪንግ ፋከልቲ ለተወጣጡ ባለሙያዎችና መምህራን በተሽከርካሪዎች አያያዝ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥተዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልጸጊያ ማዕከል ከዚህ በፊት ሲሠራ እንደቆየው ሁሉ በተማሪዎች መካከል የቢዝነስ ሃሳብ (Business Idea) ውድድር በማካሄድ አሸናፊዎችን መሸለም ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የቢዝነስ ሃሳብ (Business Idea) በማዘጋጀት መወዳደር የምትፈልጉ ተማሪዎች በውድድሩ እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል፡፡ ከምዝገባ በኋላ ስለቢዝነስ ዕቅድ አዘገጃጀት ሥልጠና የምንሰጥ መሆኑን እየገለጽን፡-

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት ከጥር 2011 ዓ/ም ጀምሮ በአርባ ምንጭ፣ ሳውላና በዩኒቨርሲቲው ኮሚዩኒቲ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ሲካሄድ የነበረው በICT መሣሪያዎች የተደገፈ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማስተማሪያ ስነ ዘዴ ማሻሻያ ግራንድ የምርምር ፕሮጀክት የመዝጊያ መርሃ ግብር ጥር 4/2015 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ