በዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ጂኦግራፊክ ኢንፎርሜሽን ሲስተም /GIS/  ሶሳይቲ ቅርንጫፍ ቢሮ ኅዳር  3/2015 ዓ/ም ተከፍቷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ፎይጫኑ

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝደንትነት ውድድር ነሐሴ 19/2014 ዓ.ም በወጣው ማስታወቂያ መሠረት የቀረቡ 13 ዕጩ ተወዳዳሪዎች የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ፣ የመምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞች እና የተማሪዎች ተወካዮች፣ የዩኒቨርሲቲው ሴኔትና ካውንስል አባላት፣ ነባር መምህራን እና ተመራማሪዎች በተገኙበት የስትራቴጅክ ዕቅዶቻቸውን ኅዳር 5/2015 ዓ.ም እያቀረቡ የሴኔት ድምፅ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ተከናውኗል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሕክምና ላይ ለሚገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት የሚውል 1.5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የብርድ ልብስና አንሶላ ድጋፍ ኅዳር 3/2015 ዓ/ም በመካላከያ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት አስረክቧል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ ::

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ከ ̋UNHCR” ጋር በጋራ በመተባበር  ከጋሞ፣ ጎፋ እና ኮንሶ ዞኖች፣ እንዲሁም ደራሼ እና አሌ ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንቶችና ም/ፕሬዝደንቶች፣ ዳኞች፣ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞች ፣ አቃቢያን ሕጎች፣ የነጻ ሕግ ድጋፍ ሰጪ ባለሙያዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ጋር  በነፃ የሕግ ድጋፍና በካምፓላ ስምምነት ዙሪያ ኅዳር 1/2015 ዓ/ም የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር 16ውን የአፍሪካ ወጣቶች ወርን ‹‹ትምህርትና የወጣቶች ስብዕና ግንባታ›› በሚል ርዕስ ኅዳር 1/2015 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው አክብረዋል፡፡ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡