አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በ2ኛ ዲግሪ መርሃ ግብሮች በመደበኛ፣ በማታ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት፣ እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 2,561 ተማሪዎችን ሰኔ 25/2014 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 662ቱ ሴቶች ናቸው፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ሰኔ 23/2014 ዓ/ም ባደረገው ስብሰባ በመጀመሪያና በ2ኛ ዲግሪ መርሃ ግብር በመደበኛ፣ በማታ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 2,540 ተማሪዎችን ቅዳሜ ሰኔ 25/2014 ዓ/ም እና እሁድ ሰኔ 26/2014 ዓ/ም እንዲመረቁ ወስኗል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 3ኛውን ሀገራዊ ዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ፎረም ‹‹የቴክኖሎጂ ሽግግርና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርን ማሳደግ›› በሚል መሪ ቃል ሰኔ 21/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የትውውቅ እንዲሁም ለቀድሞ የቦርዱ አባላት የምስጋናና የሽኝት መርሃ ግብር ሰኔ 11/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን ነባር ቅድመ-ምረቃና ድኅረ-ምረቃ ክረምት መርሃ-ግብር ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደው ሐምሌ 11 እና 12 ቀን 2014 ዓ/ም ሆኖ ትምህርት የሚጀመረው ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ/ም መሆኑን ያሳውቃል፡፡