የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል ከዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ ጉድኝትና ከተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬቶች እንዲሁም ከ STEMpower መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ከጋሞ፣ ጎፋና ኮንሶ ዞኖች እና ከደራሼ፣ ባስኬቶ፣ ቡርጂና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ 291 ከ7-12 ክፍል ተማሪዎች በኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ፊዚክስ፣ ሒሣብ፣ ኤሌክትሮኒክስና ICT ትምህርቶች ከሐምሌ 15 - ነሐሴ 30/2014 ዓ/ም የሚቆይ ሥልጠና እየሰጠ ነው፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ከ15 ዓመት በታች በሁለቱም ፆታዎች የፓይለት ፕሮጀክት ምዘና ውድድር ከሐምሌ 17-ነሐሴ 1/2014 ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ በአርባ ምንጭ ከተማ አካሂዷል፡፡

የ‹‹International Youth Fellowship (IYF)›› ሊቀ መንበርና አስተሳሰብ ቀረጻ አስተምህሮ/Mindset Education/ ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ቾው ሱንግዋ/Dr Cho Sunghwa/ ‹‹Public Lecture on Mindset›› በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የሕዝብ ገለጻ/Public lecture/ ሐምሌ 29/2014 ዓ/ም አቅርበዋል፡፡

በአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሚቲዎሮሎጂና ሃይድሮሎጂ ፋከልቲ አዘጋጅነት ‹‹Potential Collaborations on Tropical Meteorology and Climate Research Some Ideas on Multi-Disciplinary Approach›› በሚል ርዕስ ሐምሌ 22/2014 ዓ/ም ሴሚናር ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ