የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን ነባር ቅድመ-ምረቃና ድኅረ-ምረቃ ክረምት መርሃ-ግብር ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደው ሐምሌ 11 እና 12 ቀን 2014 ዓ/ም ሆኖ ትምህርት የሚጀመረው ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ/ም መሆኑን ያሳውቃል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ ከ ‹‹Social Sciences for Severe Stigmatizing Skin Conditions (5s Foundation) እና ከኢትዮጵያ ሶሲዮሎጂስቶች፣ ማኅበራዊ ሠራተኞችና አንትሮፖሎጂስቶች ማኅበር/‹‹Ethiopian Society of Sociologists, Social Workers and Anthropologists (ESSSWA) ጋር በመተባበር ከዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ከሰባቱም ት/ክፍሎች ለተወጣጡ 41 መምህራን ከሰኔ 16-18/2014 ዓ/ም በምርምር ሥነ ምግባር ላይ ያተኮረ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተቋማዊ ጥራት ግምገማ ወርክሾፕ ሰኔ 16/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ በዕለቱ በኮሌጁ በሚገኙ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ሲካሄድ የቆየው የውስጥ ኦዲት ግምገማ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጓል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና በኢትዮጵያ ባዮ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ትብብር በኢኖቬቲቭ እንሰት ፕሮጀክት አማካኝነት የተሠሩ 4 ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪ ዶ/ር አዲሱ ፈቃዱ በ 1 የፈጠራ ሥራቸው ከኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የአእምሯዊ ንብረት ማረጋገጫ /Patent/ የምስክር ወረቀት አግኝተዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ከምርምር ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ‹‹Manuscript Writing››፣ ‹‹Grant and Collaborative Proposal Writing››፣ ‹‹Digital Data Collection››፣ ‹‹Opportunities for Collaborative Projects›› በሚሉ ርዕሶች ዙሪያ ለዩኒቨርሲቲው ሴት ተመራማሪዎችና መምህራን ከሰኔ 10-11/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡