የዩኒቨርሲቲው ካውንስል ከሣይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በወረዱ አዳዲስ መመሪያዎችና የሥራ አቅጣጫዎች እንዲሁም በዘርፉ የቀጣይ 10 ዓመታት ዕቅድ ዙሪያ ጥር 5/20112 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡

ሠላማዊ የመማር ማስተማር ሂደትን ማስፈንና ማዝለቅ፣ ዩኒቨርሲቲዎችን በመስክና በተልዕኮ መለየት፣ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የትምህርትና ሥልጠና ለውጥ ሥራዎች ትግበራና ቀጣይ ሥራዎች፣ ICTን ለመማር ማስተማር፣ ለምርምርና ለተቋም አስተዳደር ማዋልና ቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች እንዲሁም የሣይንስ፣ የምርምርና የማኅበረሰብ አገልግሎት ሪፎርም አተገባበር ውይይቱ ከተደረገባቸው ዓበይት ጉዳዮች መካካል ናቸው፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

AMU has hosted 14th annual conference on ‘Role of Physics in Science Advancement and Innovative Technologies’ at New Auditorium, Main Campus, from 7th to 8th February, 2020. This conference is first of its kind for AMU and 14th in series for Ethiopian Physical Society that promotes physics as overarching science indispensable in its nature in creating scientific advancements and innovative technologies. Click here to see the pictures

የዩኒቨርሲቲው ሕግ ት/ቤት ከእንግሊዙ ኦክስፎርድ ብሩክስ /Oxford Brookes/ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመማር ማስተማር፣ በምርምርና በመምህራን ልማት ላይ በጋራ እየሠራ መሆኑን ገልጿል፡፡ በዚህም መሠረት ከኦክስፎረድ ብሩክስ ዩኒቨርሲቲ የመጡ ተማሪዎችና ፕሮፌሰሮች ከዩኒቨርሲቲው ሕግ ት/ቤት ተማሪዎች ጋር የጋራ የመስክ ትምህርት እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ-ምረቃ ትምህርት ቤት በ2012 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለተኛ መንፈቀ-ዓመት በመደበኛና በማታ እንዲሁም በሣምንት መጨረሻ መርሐ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን ተቀብሎ ማሰልጠን ይፈልጋል፡፡

icon ለበለጠ መረጃ ይህንን ይጫኑ

ከታኅሣሥ 14/2012 ዓ/ም ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የተማሪዎች ኅብረት የፓርላማ አባላትና አመራሮች ምርጫ ጥር 03/2012 ዓ/ም የኅብረቱ የሥራ አስፈጻሚ እንዲሁም የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚቴ አባላትን በመምረጥ ተጠናቋል፡፡

በዚህ መሠረት ተማሪ አንዳርጋቸው ደስታ የኅብረቱ ፕሬዝደንት፣ ተማሪ የትምወርቅ ክብሩ ም/ፕሬዝደንት እንዲሁም ተማሪ ቃልኪዳን አባይነህ ዋና ፀሐፊ በመሆን ተመርጠዋል፡፡ በተጨማሪም ተማሪ ገነት ካሳዬ፣ ተማሪ ሀለፎም ደረጀ እና ተማሪ ሚልኪያስ ሙርቴ የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚቴ አባላት ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ