የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን /ERA/ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአገሪቱ ውስጥ ከሚገኙ 7 ዩኒቨርሲቲዎች ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ከተወጣጡ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሲቪል ምህንድስና ሥር እየተሰጡ ባሉ የ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች አፈፃፀም ሂደት ላይ ኅዳር 19/2012 ዓ/ም በኃይሌ ሪዞርት ውይይት አካሂዷል፡፡Click here to see the pictures

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከቤልጂየሙ ʻKU Leuvenʼ፣ ከሲውዘርላንዱ ʻETH Zurichʼ እንዲሁም ከኬንያው ʻEldoretʼ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር ‹‹ምርምርን መሠረት ያደረገ ትምህርት ለዘላቂ የገጠር ልማት›› በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የመስክ ኮርስ ከኅዳር 8/2012 ዓ/ም ጀምሮ ለ15 ቀናት አስተናግዷል፡፡
በመስክ ኮርሱ  30 ተማሪዎችና 6 አማካሪዎች ከአ/ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ 21 ተማሪዎችና 8 ፕሮፌሰሮች ከቤልጂየሙ ʻKU-Leuvenʼ፣ 15 ተማሪዎችና 3 ፕሮፌሰሮች ከሲውዘርላንዱ ʻETH-Zurichʼ እንዲሁም 4 ፕሮፌሰሮች ከኬንያው ʻEldoretʼ ዩኒቨርሲቲ ተሳትፈዋል፡፡Click here to see the pictures

ዩኒቨርሲቲው በቁጫ ወረዳ ከፍተኛ የወተት አምራች ከሆኑ 3 ቀበሌያት ለተወጣጡ 18 ሴት ሞዴል አርሶ አደሮች ጥቅምት 29/2012 ዓ/ም ዘመናዊ የወተት መናጫ አጠቃቀም ስልጠና በመስጠት ቴክኖሎጂውን አሽጋግሯል፡፡Click here to see the pictures

የሠላም በር ኮንስትራክሽንና ኢንደስትሪያል ኮሌጅ ለትምህርት ግብዓት የሚሆን የቁሳቁስ ድጋፍ እንዲደረግለት በጠየቀው መሠረት ጥቅምት 28/2012 ዓ/ም ዩኒቨርሲቲው ሦስት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር የሚገመት የኮምፒዩተር፣ የጥቁር ሠሌዳና የወንበር ድጋፍ አድርጓል፡፡Click here to see the pictures

Arba Minch University inked agreement with Ethiopian branch of New York-based World Trade and Investment Network (WTIN) that’s assures multiple corresponding benefits for the university. This 5-year pact was signed by University President, Dr Damtew Darza and WTIN Country Director, Mr Tewodros Afrisson, at former’s office on 28th November, 2019..Click here to see the pictures