የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ መምህር፣ ታዋቂ የፈጠራ ባለቤትና በIBM ካምፓኒ ውስጥ ተመራማሪ ከሆኑት ቺፍ አርክቴክት ዶ/ር ኮሚ ወ/ማርያም ጋር አርቲፊሻል ኢንተሊጀንስን በዘላቂ የምግብ ዋስትናና ግብርናን በማዘመን ዘዴ በመጠቀም ላይ ሚያዝያ 7/2014 ዓ/ም ኦንላይን ሴሚናር አካሂዷል፡፡

በአዲሱ የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ ምርጫ መመሪያ መሠረት በ2012 ዓ.ም የተመረጠው የተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ ሁለት ዓመት የሥራ ዘመን መጠናቀቁን ተከትሎ በአዲስ አባላት ለመተካት ከታኅሣሥ 8/2014 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የዋና ሥራ አስፈፃሚ ምርጫ ሂደት ሚያዝያ 02/2014 ዓ.ም ተጠናቋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሰላም ፎረም አባላትና የ2014 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች ‹‹በፍቅር በመደመር ሰላማችንን እንጠብቅ›› እና ‹‹100 ቀናችንን በጽዳት ዘመቻና ችግኞችን ውሃ በማጠጣት እናሳልፍ›› በሚሉ መሪ ቃሎች በዋናው ግቢ የጽዳት ዘመቻና ችግኝ ውሃ የማጠጣት መርሃ-ግብር አካሂደዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-ትምህርትና ሥነ-ባህሪ ሳይንስ ት/ቤት ለጊዶሌ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችና መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች የምልክት ቋንቋ ምንነት፣ የአካቶ ትምህርት ጽንሰ ሃሳብና አተገባበር፣ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች የማስተማሪያ ሥነ-ዘዴና ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች የሚያስፈልጋቸው ጭብጦች ዙሪያ ከመጋቢት 14-15/2014 ዓ/ም በልዩ ፍላጎትና አካቶ ት/ክፍል መምህራን ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ፊዚክስ ት/ክፍል ከጋሞ ዞን ወረዳዎች ለተወጣጡ 29 የፊዚክስ መምህራን በኅዋ ሳይንስ ምርምር ዙሪያ እንዲሁም ለት/ክፍሉ የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች የምርምር ጽሑፍ አዘገጃጀትን አስመልክቶ ከመጋቢት 14-17/2014 ዓ/ም የቆየ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡