በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት በትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔ በ2014 የትምህርት ዘመን ወደ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ፡-

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩትነት ከተቋቋመበት ከ1979 ዓ/ም ጀምሮ ለአርባ ምንጭ ከተማ፣ ለጋሞ ዞንና የዞኑ ወረዳዎች፣ አጎራባች ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች እንዲሁም ከተማ አስተዳደሮች ከመደበኛው መማር ማስተማርና ምርምር ጎን ለጎን በማኀበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ እያገለገለ ቆይቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል ‹‹የብዕር ጥበብ›› አስተዋይ ወጣት ለኢትዮጵያ አንድነት በሚል ርዕስ ሚያዝያ 8/2014 ዓ/ም የኪነ ጥበብ ፕሮግራም አካሂዷል፡፡ በፕሮግራሙ ጋዜጠኛና ደራሲ ዘነበ ወላ፣ ደራሲ መሐመድ አሊ (ቡርሃን አዲስ) እና የጋሞ አባቶች በተጋባዥ እንግድነት ተገኝተዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ለባልታ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለመማር ማስተማር ሥራ የሚውሉ የባዮሎጂ፣ የኬሚስትሪና የፊዚክስ ቤተ-ሙከራ ኬሚካሎችና ቁሳቁሶችን ሚያዝያ 8/2014 ዓ/ም ድጋፍ አድርጓል፡፡ ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን 130,000 (አንድ መቶ ሠላሳ ሺህ) ብር የሚያወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡