በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂና ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች በምርምር፣ በማኅበረሰብ አገልግሎትና በኢንደስትሪ ትስስር ዘርፎች በተከለሰ መመሪያ ዙሪያ ሰኔ 25/2014 ዓ/ም ውይይት ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በኢትዮጵያ የኢንዶኔዢያ አምባሳደር አል ቡስራ ባስኑር (Al Busyra Basnur) በግብርናው ዘርፍ በተለይ እምቦጭን ከመከላከልና የአኩሪ አተር ምርትን ከማሻሻል ጋር በተያያዘ የሀገራቸውን ተሞክሮ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰኔ 23/2014 ዓ/ም ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ ምሁራን፣ ተመራማሪዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አድርገዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ከተማ ሥራ ዕድል ፈጠራ ኢንተርፕራይዝ ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና ከ‹‹UNDP›› ፕሮግራም ጋር በመተባበር ከከተማዋ የተወጣጡ ወጣቶች ባቀረቡት የሥራ ፈጠራ ላይ ሰኔ 23/2014 ዓ/ም ውድድር አካሂዷል፡፡ ውድድሩ በጽንሰ ሃሳብ ማብራሪያ የቀረበ ሲሆን የተወሰኑት በተግባር የተደገፉ ማሳያዎችን አቅርበዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ለቴክኖሎጂና ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ተመራቂ ተማሪዎች በሥነ-ምግባርና በሙስና ወንጀሎች ዙሪያ ሰኔ 20/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

አርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የ‹‹Ethio Jobs›› አጋር ድርጅት ከሆነው ‹‹Derja.com›› ጋር በመተባበር ለ2014 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች ‹‹Self Discovery››፣ ‹‹Building Self Image››፣ ‹‹Communication at the Work Place››፣ ‹‹Analytical Thinking››› በሚሉና ሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ ከሰኔ 17-21/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡