- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከ‹‹AMU-IUC›› ፕሮጀክት V ጋር በመተባበር ‹‹Evidence-based Training for Model Farmers and Stakeholders on Solutions to Challenges of Enset Production and Livestock Feed Security in Gamo Zone, Southern Ethiopia›› በሚል ርእስ ከጋሞ ዞን ሰባት ወረዳዎች ለመጡ አርሶ አደሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች ከሐምሌ 05-08/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበው የመጡ የመጀመሪያ ዙር የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች፣ ፈታኞች፣ የፈተና አስፈጻሚዎችና አስተባባሪዎች ቅበላና አጠቃላይ የፈተና አሰጣጥ ገለጻ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በስድስቱም ካምፓሶቹ 11,773 ወንድ እና 12,354 ሴት በድምሩ 24,127 ተማሪዎች የተቀበለ ሲሆን በትምህርት ሚኒስቴር መርሃ ግብር መሠረት ፈተናውን ከሐምሌ 19/2015 ዓ/ም ጀምሮ የሚወስዱ ይሆናል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ቅድመ ዝግጅት አጠናቀቀ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከራእይ ፕሮጀክት እና ከአርባ ምንጭ ከተማ ሴቶችና ሕፃናት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከውሃ ምንጭ ቀበሌ ሃይላንድ መንደር ለተወጣጡ በእንጨት ለቀማ ለሚተዳደሩና በፕሮጀክቱ ለታቀፉ 91 ሴቶች ሐምሌ 7/2015 ዓ/ም የሕይወት ክሂሎትና ሥራ ፈጠራ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: በእንጨት ለቀማ ለሚተዳደሩ በፕሮጀክት የታቀፉ ሴቶች የሕይወት ክሂሎትና ሥራ ፈጠራ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
አቶ ፍሬው ዳንኤል ከአባታቸው ከአቶ ዳንኤል ሻሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አማረች ጸላ በቀድሞው ጋሞ ጎፋ አውራጃ አርባ ምንጭ ወረዳ ቆላ ሼሌ ቀበሌ በ1976 ዓ/ም ተወለዱ፡፡
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ያሠለጠናቸውን 74 ወንድና 21 ሴት በድምሩ 95 ተማሪዎች ለ6ኛ ጊዜ ሐምሌ 14/2015 ዓ/ም አስመርቋል። ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ያሠለጠናቸውን ተማሪዎች ለ6ኛ ጊዜ አስመረቀ