የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ሐምሌ 10/2015 ዓ/ም በቤሬ ተፋሰስ ላይ ከ10 ሺህ በላይ ችግኞችን በመትክል በ5ው ዙር የአረንጓዴ አሻራና በአንድ ጀምበር 500 ሚሊየን ችግኞችን የመትከል መርሃ ግብር ላይ ተሳትፎ አድርጓል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለመርሃ ግብሩ ባሉት ዘጠኝ የችግኝ ጣቢያዎች ከአንድ ሚሊየን በላይ ችግኞችን አዘጋጅቶ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎች እየተሰራጨ ይገኛል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

AMU - IUC Project V organized Four Day evidence-based training on sustainable solutions to challenges of Enset production and livestock feed security for 73 model farmers and stakeholders from 7 Wordas of Gamo Zone, from July 12-15, 2023. Click here to see more Photos.

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ በመደበኛ፣ በማታ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ የማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የሕግ ት/ቤት እንዲሁም የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና የሳውላ ካምፓስ ተማሪዎችን እንዲሁም በሁሉም ኮሌጆችና ፕሮግራሞች በ2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ ያሠለጠናቸውን ተማሪዎች ሐሙስ ሐምሌ 13/2015 ዓ/ም በዋናው ግቢ አዲሱ አዳራሽ እና ዓርብ ሐምሌ 14/2015 ዓ/ም በሳውላ ካምፓስ  በደማቅ ሁኔታ የሚያስመርቅ ይሆናል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 7/2015 ዓ/ም ድረስ ሲሰጥ የነበረው የ2015 ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና/Exit –Exam/ በስኬት ተጠናቀቀ፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

‹‹ነገን ዛሬ እንትከል!›› በሚል መሪ ቃል 5ኛው ዙር ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 10/2015 ዓ/ም ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ ሁሉንም የዩኒቨርሲቲውንና የአካባቢውን ማኅበረሰብ በማሳተፍ ይጀመራል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ