በጥናትና ምርምር ተደግፎ ለኢትዮጵያውያን ሕጻናት፣ መምህራንና ወላጆች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ንባብ ክሂል ለመማሪያና ለማስተማሪያ የሚሆን “Easy Ways to Read in English” ወይም “የእንግሊዝኛ ቋንቋ ፍኖተ-ንባብ” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ታኅሣሥ 26/2014 ዓ/ም ከጧቱ 02፡30 ጀምሮ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት፣ የእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ት/ክፍል መምህራን፣ ተጋባዥ እንግዶች፣ የጋሞ ዞንና በዞኑ የሚገኙ ወረዳዎች የትምህርት ሴክተር ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ መግቢያ በር አካባቢ በሚገኘው አዳራሽ የውይይትና የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ይካሄዳል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፌዴራል የፍትሕ እና የሕግ ምርምርና ሥልጠና ኢንስቲትዩት እና ከኢትዮጵያ የሕግ ት/ቤቶች ማኅበር ጋር በመተባበር ‹‹Contemporary Challenges, Trends and Governance of Internally Displaced Persons Protection in Ethiopia›› በሚል ርዕስ 2ኛውን ዓመታዊ የምርምር ጉባዔ አካሂዷል፡፡ በጉባዔው ከተለያዩ የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት በመጡ ምሁራን ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የሕግ ት/ቤት በሽግግር ፍትሕ አማራጮች ያለፉ ጉዳዮች መፍታት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ የዩኒቨርሲቲው ሕግ ተማሪዎች፣ መምህራንና ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ የተወጣጡ ግለሰቦች በተገኙበት ታኅሣሥ 12/2014 ዓ/ም ሴሚናር አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማኅበር 28ኛው ሀገር አቀፍ ኮንፍራንስ ላይ ከቀረቡ ሳይንሳዊ የምርምር ውጤቶች ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቅ ሀና እንዳሻውና በማስተርስ ዲግሪ ምሩቅ ሁሴን አሊ የላቀ የመመረቂያ ጽሑፍ በማቅረብ ታኅሣሥ 9/2014 ዓ/ም ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡

በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የኤሌትሪካል እና ኮምፕዩተር ምኅንድስና ፋከልቲ መምህር፣ ተመራማሪና አማካሪ የሆኑት ዶ/ር አንቺት ቢጀልዋን (Dr Anchit Bijalwan) ‹‹Network Forensics፡ Privacy and Security›› በሚል ርዕስ 2ኛ መጽሐፋቸውን አሳትመዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ