የኤፌዴሪ ፕሬዝደንት ክብርት አምባሳደር ሣህለወርቅ ዘውዴ ጥቅምት 12/2013 ዓ/ም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተገኙበት ዩኒቨርሲቲው ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ካላቸው ቤተሰቦች የሚመጡ የ1ኛ ዓመት ተማሪዎች የትምህርት ድጋፍ እንዲያገኙ ከተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ከግብርና ሳይንስ ኮሌጅ እንዲሁም ከብራይት ፊውቸር አግሪካልቸር /BFA/ የደቡብ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ‹‹የሥርዓተ ፆታ ግንዛቤ፣ አካታች ጽንሰ ሀሳቦችና ዘዴዎቹ›› በሚል መሪ ቃል በሥራ ክፍሉ ለሚገኙ ባለሙያዎች እና ከተለያዩ ተቋማት ለተወጣጡ ባለድርሻ አካላት ከጥቅምት 09/2013 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 5 ቀናት ስሲጥ የነበረው የአሠልጣኞች ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

The University seeks competent, committed and interested Ethiopian academic staff to assign for the Deanship position for college of Agricultural Sciences.

icon Advertisement for Deanship Position of College of Agricultural Sciences-2013

በ2012 ዓ/ም ሊሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ የሕግ መውጫ ፈተና (Exit Exam) በኮቪድ-19 መከሰት ምክንያት ወደ 2013 ዓ/ም መተላለፉ ይታወሳል፡፡

ስለሆነም ፈተናው የሚሰጠው ከኅዳር 1-4/2013 ዓ/ም በመሆኑ ፈተናውን መውሰድ የምትፈልጉ በሙሉ ከጥቅምት 2-12/2013 ዓ/ም ድረስ ብቻ ብር 664.00 ( ስድስት መቶ ስልሳ አራት ብር ብቻ) በኤጀንሲው የባንክ ሒሳብ ቁጥር 0171597578400 ገቢ ያደረገባችሁበትን ደረሰኝ በመያዝ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ቀርባችሁ መመዝገብ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡