የሳሃይ ሶላር ፕሮጀክት የፋይዳ ዳሰሳ ጥናት ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የካቲት 14/2013 ዓ/ም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ፕሮጀክቱ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ በቀደሞው ጋሞ ጎፋ ዞን፣ በUniversity of Applied Sciences and Arts of Southern Switzerland እና በሳሃይ ሶላር ማኅበር እ.ኤ.አ በ2015 በተፈረመ የትብብር ስምምነት መሠረት የተከናወነ ሲሆን በእስከ አሁን ቆይታው 23 ጤና ጣቢያዎችንና 6 ት/ቤቶችን የ24 ሰዓት የፀሐይ ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ማድረጉ በዳሰሳ ጥናቱ ተመልክቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ከሰው ሀብት ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት፣ ከለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት እና ከማኔጅመንት ት/ክፍል ጋር በመተባበር ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተወጣጡ አገልግሎት ሰጪ ሠራተኞች በደንበኛ አያያዝና ጥራት ያለው አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከየካቲት 10-11/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት በነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት የሥራ አፈፃፀምና ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎች ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ከነፃ የሕግ ድጋፍ ማዕከላት አስተባባሪዎችና ከት/ቤቱ መምህራን ጋር የካቲት 12/2014 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአገሪቱን መረጃና የመረጃ መሠረተ ልማቶች ለመጠበቅ የሚያስችል አቅም በመገንባት የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የማስጠበቅ ተልዕኮን አንግቦ እየሠራ የሚገኘው የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ /INSA/ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመስኩ የሠለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት እንዲሁም በምርምርና ልማት ሥራዎች ላይ በትብብር ለመሥራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ የካቲት 10/2014 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ/ም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ጥር 27/2014 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ