የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ነሐሴ 4/2013 ዓ/ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ለ 3 መምህራን የተባባሪ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሰጠ ሲሆን በሌሎች የተለያዩ ጉዳዩችም ላይ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ከኮሌጁ ዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት፣ ከጂኦግራፊና አካባቢ ጥናት ት/ክፍል እንዲሁም ከጀርመን ተራድኦ ድርጅት (GIZ) ጋር በመተባበር ከጋሞ ዞን ወረዳዎች ለተወጣጡ የተፈጥሮ ሀብትና ደን ልማት ባለሙያዎች በ‹‹Geographic Information System(GIS) እና ‹‹Global Positioning System››(GPS) ሶፍትዌሮች ዙሪያ ከሐምሌ 26 - ነሐሴ 1/2013 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በዩኒቨርሲቲው የሕግ ትምህርት ቤት ለሚማሩ 59 የ5ኛ ዓመት የሕግ ተመራቂ ተማሪዎች እንዲሁም ከዚህ ቀደም በተለያዩ ቦታዎች የሕግ ትምህርታቸውን ተከታትለው የመውጫ ፈተናውን ላላለፉ 87 ተማሪዎች ከሐምሌ 27-30/2013 ዓ/ም የ2013 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የሕግ መውጫ ፈተና ተሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ቤት በ2014 የትምህርት ዘመን በመደበኛ፣ በማታ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ-ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን ከዚህ በታች በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች ተቀብሎ ማሠልጠን ይፈልጋል፡፡

በጫሞ ሐይቅ ዙሪያ ለሚሠራው አሳታፊ ዘላቂ የመሬትና የውሃ አያያዝ ሥራ ዕቅድ አዘገጃጀት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ከ10 ወረዳዎች ለተወጣጡ 58 የልማት ጣቢያ ሠራተኞችና የዘርፉ ባለሙያዎች ከሐምሌ 13/2012 ዓ/ም ጀምሮ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዓባያ ካምፓስ ለ7 ቀናት ተሰጥቷል፡፡ ሥልጠናው በጀርመን ልማት ተራድኦ ድርጅት/GIZ/ እና በግብርና ሚኒስቴር የዘላቂ መሬት አያያዝ ፕሮጀክት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ያዘጋጁት ነው፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ