አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቪታ/Vita/ ከተሰኘ መንግሥታዊ ካልሆነ ድርጅት የተሻሻሉና ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችን በጋሞ ዞን ለሚገኙ ማኅበረሰቦች ለማዳረስ በሚሠራው ፕሮጀክት ዙሪያ በጋራ ለመሥራት ሚያዝያ 28/2014 ዓ/ም ለ5 ዓመታት የሚቆይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ እና ከአርባ ምንጭ ከተማ ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በከተማው ስድስት ቀበሌያት ውስጥ ከሚገኙ 12 ቀጠናዎች ለተወጣጡ 66 አመራሮችና 80 የአርባ ምንጭ ከተማ ወጣቶች አደረጃጀት አባላት ሚያዝያ 27/2014 ዓ/ም የአመራርነት ክሂሎት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ከ‹‹National Institute of Technology›› ጋር በተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት ‹‹Application of Novel Techniques for Waste Water Treatment›› በሚል ርዕስ ሚያዝያ 21/2014 ዓ/ም ኦንላይን ሴሚናር አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በ2014 የትምህርት ዘመን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ግንቦት 1 እና 2 ሲሆን ምዝገባ የሚካሄደው ግንቦት 3 እና 4 እንዲሁም ትምህርት የሚጀመረው ግንቦት 5 ቀን 2014 ዓ.ም ይሆናል፡፡

በመሆኑም ወደ ዩኒቨርሲቲው በምትመጡበት ጊዜ፡- 

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልጸጊያ ማዕከል በላንቴ ቀበሌ በማኅበር ተደራጅተው ለሚሠሩ፣ የግል ሥራ ፈጥረው ለሚንቀሳቀሱና ሥራ አጥ ለሆኑ ወጣቶች በመሠረታዊ የሥራ ፈጠራ አመለካከትና ክሂሎት ዙሪያ ሚያዝያ 10/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡