የዩኒቨርሲቲው ማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ከጋሞ ዞን ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር ከጋሞ ዞን እና በዞኑ ከሚገኙ 14 ወረዳዎችና 4 ከተማ አስተዳደሮች ለተወጣጡ 37 የቋንቋ ጥናት ባለሙያዎች እንዲሁም ለወረዳና ከተማ አስተዳደር ኃላፊዎች ከሚያዝያ 4 - 7/2013 ዓ/ም በቋንቋ ጥናት ዘዴዎች፣ በመረጃ አሰባሰብ ሂደት፣ በስነ-ቃል እና በስነ-ጽሑፍ ጥናት ላይ ያተኮረ የክሂሎት ማሻሻያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት በዓለም ለ110ኛ በኢትዮጵያ ለ45ኛ ጊዜ የተከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ‹‹የሴቶችን መብት የሚያከብር ማኅበረሰብ እንገንባ›› በሚል መሪ ቃል መጋቢት 30/2013 ዓ/ም በሳውላ ካምፓስ አክብሯል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ብራይት ፊውቸር አግሪካልቸር ፕሮጀክት /BFA/ ‹‹የሥራ ፈጠራ ክሂሎትን ማሳደግ›› በሚል ርዕስ ከተለያዩ ክልሎች የግብርና እና ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኮሌጆች ለተወጣጡ መምህራን ከመጋቢት 23/2013 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 8 ቀናት የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶ/ር ይስሃቅ ከቸሮ እንደተናገሩት ሠልጣኞች በራሳቸው ዘርፍ ሥራ እንዲፈጥሩና ለተማሪዎቻቸውም ማሳየት እንዲችሉ ክሂሎታቸውን ለማሳደግ የተዘጋጀ ሥልጠና ነው፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በውሃ አቅርቦትና ሳኒተሪ ምኅንድስና የ3ኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራም ለማስጀመር ሚያዝያ 2/2013 ዓ/ም የሥርዓተ ትምህርት የውስጥ ግምገማ አካሂዷል፡፡

የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር ዓለማየሁ ጩፋሞ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው የምርምር ዩኒቨርሲቲ ተብሎ እንደመለየቱ በ2ኛና 3ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች በትኩረት እየሠራ ይገኛል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት 5 ዓመታት 5,000 የ3ኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ለማስመረቅ ያቀደ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ፕሮግራሙን መክፈቱ ለዚህ ሀገራዊ ዕቅድ መሳካት የበኩሉን አስተዋፅኦ የሚያበረክትበት ዕድል የሚፈጥር ነው፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Arba Minch University has signed a general Memorandum of Understanding with Geological Survey of Ethiopia (GSE) to collaborate in the field of research, academia, mining, exploration, capacity building, and exchange of expertise in identified areas for the span of 5-year in Gamo and Gofa Region. AMU President, Dr Damtew Darza, GSE Director General, Mrs Enatfenta Melaku, and Deputy Director General, Dr Dejene Hailemariam, inked the agreement in the presence of officials from both parties at President’s Office on 5th April, 2021. Click here to see the pictures