በአርባ ምንጭ ዪኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የሥነ-ትምህርትና ሥነ-ባህሪ ትምህርት ክፍል ከእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር <<English for Secretaries>> በሚል ርዕስ ለቢሮ ፀሐፊዎችና ረዳቶች በዋናዉ ግቢ መጋቢት 30/2013 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ጋር በመተባበር በዞኑ ከሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተወጣጡ መምህራን በቤተ-ሙከራ አጠቃቀምና አተገባበር ዙሪያ ከሚያዝያ 26/2013 ዓ/ም ጀምሮ ለ5 ተከታተይ ቀናት የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጋሞ ዞን ገቢዎች ባለሥልጣን ቅ/ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከ12 ወረዳዎች ለተወጣጡ የICT ባለሙያዎች በኔትወርኪንግና በቢሮ ማሽኖች ጥገና ላይ ከሚያዝያ 14-19/2013 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ተወካይ ዶ/ር ሙሉነህ ለማ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው በምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች ላይ በትኩረት እየሠራ መሆኑን ተናግረው የዚህ ዓይነት ሥልጠናዎችም የዚሁ ሥራ አካል ናቸው ብለዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በገረሴ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ነፃ የማሕፀን ውልቃት ቀዶ ጥገና አገልግሎት ሚያዝያ 19/2013 ዓ/ም ሰጥቷል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማሕፀንና ጽንስ ስፔሻሊስት ዶ/ር ነጋ ጩፋሞ ዩኒቨርሲቲው ትኩረት ሰጥቶ ከሚያከናውነው የመማር ማስተማር ሥራዎች ባሻገር በየዘርፉ የማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራዎችን እንደሚሠራ ተናግረው የማሕፀን ውልቃት በሽታ እየሰፋ ከመጣባቸው አካባቢዎች ገረሴና አካባቢው አንዱ በመሆኑን ጠቅሰው የገረሴ አጠቃላይ ሆስፒታል ዩኒቨርሲቲውን ትብብር በመጠየቁ አገልግሎቱ መሰጠቱን ጠቁመዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

In this pandemic-hit situation where people are losing jobs in fast succession and life has became difficult for many, Community Service Directorate has started creating jobs and infusing entrepreneurial spirit in youth to make them self-reliant, informed Director, Dr Teklu Wegayehu; as of now, we may be at fledgling stage, but future ahead holds great possibilities and ample opportunities.  Click here to see the pictures