የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ጽ/ቤት በስሩ ከሚገኙ ኢንስቲትዩቶች፣ ኮሌጆች፣ ትምህርት ቤቶችና ሌሎች የሥራ ክፍሎች ጋር የ2016 ዓ/ም ዕቅድ የውል ስምምነት ጥቅምት 26/2016 ዓ/ም ተፈራርሟል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

Addis Ababa University in collaboration with the Ministry of Education has scheduled to administer the National Graduate Admission Test (NGAT) in selected exam centers again; therefore, those who didn’t pass the past NGAT and interested new examinees can register online and take the test according to the following schedule.

  1. Registration for the National Graduate Admission Test at the AAU portal is open on Monday
     - Friday (November 6-10, 2023);
  2. Exam administration is on the following week Monday-Friday (November 13-17, 2023).

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከክርስቲያን ኤይድ/Christian Aid/ ጋር በመተባበር በጋሞ ዞን ካምባ ዙሪያ ወረዳ ዲንጋሞ ቀበሌ በማይጸሌ ወንዝ ላይ እያስገነባ ለሚገኘው ፒኮ ሃይድሮፓወር ፕሮጀክት የሚውሉና ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ተርባይን፣ ጄኔሬተርና የኤሌክትሪክ መቆጣጠሪያ ከሕንድ ሀገር ጥቅምት 22/2016 ዓ/ም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ደርሰዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በገቢዎች ሚኒስቴር የሀዋሳ ቅ/ጽ/ቤት ለአርባ ምንጭና ጂንካ ዩኒቨርሲቲዎች የፋይናንስና ግዥ ባለሙያዎች፣ ኦዲተሮች እና የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎች በታክስ ሕግና መመሪያ ዙሪያ ጥቅምት 15/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የ2016 ትምህርት ዘመን የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና /National Graduate Admission Test – NGAT/ ያለፋችሁ እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ ማታ እና ሳምንት መጨረሻ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር የምትፈልጉ አመልካቾች ከሰኞ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ዓርብ ጥቅምት 23/2016 ዓ/ም ባለው ጊዜ ውስጥ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አሉምናይ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 210 እና 211 ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን፡፡