Arba Minch University expatriate instructor, Dr Vishnu Narayanan Vishwanathan Pillai, resident of Kannur district in Kerala, India, was killed along with driver when the private car they were travelling in collided head-on with the public bus coming from Addis Ababa at Sankura woreda, Silte Zone, Ethiopia at 3 pm on 12th June, 2021.

በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ‹‹ድምጻችን ለነፃነታችንና ለሉዓላዊነታችን›› በሚል መሪ ቃል አገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በጋራ ድምጽ የሚያሰሙበት የበይነ-መረብ መርሃ-ግብር ሰኔ 3/2013 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም በፕሮግራሙ ተሳትፈዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ባዮሎጂ ትምህርት ክፍል በ‹‹Biodiversity Conservation and Management›› የትምህርት ፕሮግራም ለመጀመሪያ ጊዜ በ3ኛ ዲግሪ ለማስመረቅ የሚያስችለውን ቅድመ ሁኔታ አጠናቋል፡፡ ዕጩ ተመራቂ ሙላቱ ኦሴ ለምረቃ ብቁ የሚያደርገውን ጥናታዊ ጽሑፍ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ምሁራን በተገኙበት ሰኔ 04/2013 ዓ/ም አቅርቧል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ አስመልክቶ በትምህርት ጥራትና አግባብነት ዙሪያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ፕሮፌሰሮች ካውንስልና ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተፎካካሪ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ ሰኔ 05/2013 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ለጨንቻ ወረዳ ሆሎኦ ላካ ሙሉ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ሰኔ 3/2013 ዓ/ም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡