ከዛሬ ኅዳር 27/2014 ዓ/ም ጀምሮ ሪፖርት በማድረግ ትምህርት እንድትጀምሩ አጥብቀን እናሳስባለን፡፡

የሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለሚያስተምሩ ነባር የሕክምና መምህራን ‹‹Case Based Discussion›› በተሰኘ የሕክምና ትምህርት ማስተማሪያና የምዘና ዘዴ ላይ ከኅዳር 27 - ታኅሳስ 1/2014 ዓ/ም ለ5 ተከታታይ ቀናት ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ የኬዝ አፃፃፍ ዘዴዎች እና ኬዞችን ተጠቅሞ ተማሪዎችን ማስተማርና መመዘን የሥልጠናው የትኩረት ነጥቦች ናቸው፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

16ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ‹‹ወንድማማችነት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት›› በሚል መሪ ቃል ኅዳር 29/2014 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተከብሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ በ ‹‹ArcGIS and Remote Sensing›› ሶፍትዌር አጠቃቀም ዙሪያ 2ኛና 3ኛ ዲግሪ ላላቸው መምህራን እንዲሁም የድኅረ ምረቃ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች ኅዳር 23/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-ትምህርትና ሥነ-ባህሪ ሳይንስ ት/ቤት የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ከተማ 4 የግል ት/ቤቶች ለተወጣጡ መምህራን የግምገማ አሰጣጥና የምዘና ሂደት፣ ስሜትን የመረዳትና የማንበብ ብቃት፣ ሙያዊ ፍቅር፣ የማስተማሪያ ሥነ-ዘዴና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከኅዳር 17-18/2014 ዓ.ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ