አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ባዮቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩትና በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በሀገር አቀፍ ደረጃ በተደረገ የእንሰት ቴክኖሎጂዎች ፈጠራ ወድድር በኢኖቬቲቭ እንሰት ፕሮጀክት በተሠሩ የፈጠራ ሥራዎች ተወዳድሮ አሸናፊ መሆን ችሏል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የቀድሞ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በሚኒስትር ማዕረግ የተፈጥሮ ሀብትና የምግብ ደኅንነት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሳኒ ረዲ፣ የዘላቂ መሬት አያያዝ ብሔራዊ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ ኃይሉ፣ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ሚያዝያ 23/2013 ዓ/ም በአዲስ አበባ ውይይት ተካሂዶ የጫሞ ተፋሰስን ለማዳን አስፈላጊው ሥራ በአፋጣኝ እንዲጀመር ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዪኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የሥነ-ትምህርትና ሥነ-ባህሪ ትምህርት ክፍል ከእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር <<English for Secretaries>> በሚል ርዕስ ለቢሮ ፀሐፊዎችና ረዳቶች በዋናዉ ግቢ መጋቢት 30/2013 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ጋር በመተባበር በዞኑ ከሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተወጣጡ መምህራን በቤተ-ሙከራ አጠቃቀምና አተገባበር ዙሪያ ከሚያዝያ 26/2013 ዓ/ም ጀምሮ ለ5 ተከታተይ ቀናት የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጋሞ ዞን ገቢዎች ባለሥልጣን ቅ/ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከ12 ወረዳዎች ለተወጣጡ የICT ባለሙያዎች በኔትወርኪንግና በቢሮ ማሽኖች ጥገና ላይ ከሚያዝያ 14-19/2013 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ተወካይ ዶ/ር ሙሉነህ ለማ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው በምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች ላይ በትኩረት እየሠራ መሆኑን ተናግረው የዚህ ዓይነት ሥልጠናዎችም የዚሁ ሥራ አካል ናቸው ብለዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ