የአፍሪካ ወጣቶች ወር በአፍሪካ ደረጃ “Breaking the Barriers to Meaningful Youth Participation and Inclusion in Advocacy” በሚል መሪ ቃል ከኖቨምበር 01/2022 እ.ኤ.አ ጀምሮ እየተከበረ የሚገኝ ሲሆን በሀገራችን ደግሞ በነገው ዕለት ከጧቱ 02፡30 ጀምሮ በዋናው ግቢ በሚገኘው ትልቁ አዳራሽ “ንቁ የወጣቶች ተሳትፎና ተካታችነት ለስብዕና ልማት” በሚል መሪ ቃል ለ16 ጊዜ  ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር የወጣቱን ግንዛቤ፣ ተሳትፎና ስብዕና በሚገነባ መልኩ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች የሚከበር ይሆናል፡፡  በልዩ ትኩረት በትምህርትና ስብዕና ልማት፣ ወጣትና ሥራ ፈጣሪነት፣ የወጣቶች ተዋልዶ ጤናና ስብዕና ልማት እና አደንዛዥ ዕጽ በወጣቶች ስብዕና ላይ የሚያስከትለው ተጽዕኖና ሌሎችም የውይይት ጉዳዮች የተካተቱበት ይሆናል፡፡

Arba Minch University congratulates and wishes all the best to Pal Mai Deng, AMU post graduate Masters of Business Administration (MBA) 1st year foreign student, on his current government appointment as the Minister for Water Resources and Irrigation in the Republic of South Sudan. He is one of the foreign students who got Master’s Degree Scholarship in MBA program and joined Arba Minch University in the year 2021. To See more Pictures Click here.

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና  ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ ጉድኝት ማ/ጽ/ቤት በአርባ ምንጭ ከተማ እና አጎራባች ቀበሌያት በፈሳሽና ደረቅ ሳሙና አዘገጃጀት ሥራ ላይ ለተደራጁ 6 ማኅበራት ለሥራው የሚያግዙ የአላቂና ቋሚ ቁሳቁስ ድጋፍ ጥቅምት 17/2015 ዓ/ም አድርጓል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በባዮሎጂ ትምህርት ክፍል «Bio Diversity Conservation and Management» ትምህርት ፕሮግራም ላላፉት 5 ዓመታት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩት እጩ ዶ/ር ተመስገን ዲንጋሞ የምርምር ሥራቸውን ጥቅምት 21/2015 ዓ/ም የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርበው ተገምግሟል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ማዕከል ማስ/ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ጋር በመተባበር ከሆስፒታሉ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች በወባ በሽታ ምርመራና ሕክምና አሰጣጥ አዳዲስ አሠራሮች ዙሪያ ከጥቅምት 18-19/2015 ዓ/ም የሁለት ቀናት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡