የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ማዕከል ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ  ጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከወረዳው ጤና ጣቢያዎች ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች በአዲሱ የኤች አይ ቪ ምርመራ አልጎሪዝም /HIV Testing Algorithm/ እና በወባ በሽታ ሕክምናና ምርመራ አዳዲስ አሠራሮች /Malaria Technical Update/ ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ግንቦት 4/2016 ዓ/ም ተጠናቋል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ለዩኒቨርሲቲው ሴት መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች የአመራርነት እና የአስተዳደር ክሂሎት ሥልጠና ሚያዝያ 22/2016 ዓ/ም ሰጥቷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ የ2015/16 የሥራ ዘመን መጠናቀቁን ተከትሎ ለ2017/18 ለሁለት ዓመት የሚያገለግሉ አዲስ ሥራ አስፈጻሚዎች ምርጫ ከግንቦት 3/2016 ዓ/ም ጀምሮ እየተካሄደ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

መጋቢት 29/2007 ዓ/ም የመሠረት ድንጋይ የተጣለለት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፊታችን ሰኔ 01/2016 ዓ/ም ተመርቆ ወደ አገልግሎት ሊገባ ቀጠሮ ተይዞለታል፡፡

የአርባ ምንጭ ውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ለመጡ ባለሙያዎች ምርትና ምርታማነትን መደገፍ በሚያስችሉ የግብርና ቴክኖሎጂና ሞዴሎች ዙሪያ “Decision Support System for Agro-technology Transfer/DSSAT” በሚል ርዕስ ከሚያዝያ 16-19/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡