- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ምርምር ማዕከል ጀርመን ሀገር ከሚገኘው ሳሃይ ሶላር አስሶሴሽን ጋር በመተባበር በጋሞ ዞን ቆጎታ ወረዳ በቆጎ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 3.5 ሚሊየን ብር ያሰራው 5 ኪሎ ዋት የሚያመንጭ የሶላር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች በተገኙበት የካቲት 5/2018 ዓ/ም ተመርቋል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በቆጎታ ወረዳ 3.5 ሚሊየን ወጪ የተደረገበት የሶላር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመረቀ
- Details
የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለዩኒቨርሲቲው የማስተማሪያና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአገልግሎት ክፍል ኃላፊዎችና የጥራት ተጠሪዎች ከየካቲት 3-5/2018 ዓ/ም የአገልግሎት ጥራት ማሻሻያ ሥልጠና ሰጥቷል።ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢፌዴሪ የቅርስ ጥናትና ምርምር ባለሥልጣን፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እና ከጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር ‹‹ጋሞ ዱቡሻ ዎጋ››ን በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስንና ባህል ተቋም (ዩኔስኮ/UNESCO) በማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ በሚደረገው ሒደት ለተቋሙ የሚላኩ ሰነዶች ግምገማ እና ቀጣይ ሥራዎች ላይ የካቲት 4/2018 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ወርክሾፕ ተካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: ‹‹ጋሞ ዱቡሻ ዎጋ››ን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ የተዘጋጁ ሰነዶች ግምገማ ወርክሾፕ ተካሄደ
- Details
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም አባል በሆኑት አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ጂንካና ዲላ ዩኒቨርሲቲዎች ተግባራዊ የሚደረግ በክልሉ የሚገኙ ሕዝቦችን ሀገር በቀል ዕውቀቶች መሰነድን ዓላማ ያደረገ የትብብር ፕሮጀክት ዛሬ የካቲት 3/2018 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲዎቹ የሥራ ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች፣ ከክልሉ ባህልና ስፖርት ቢሮ፣ ትምህርት ቢሮ እንዲሁም ብሔረሰቦች ምክር ቤት የተወጣጡ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ ሀገር በቀል ዕውቀቶችን መሰነድ የሚያስችል የትብብር ምርምር ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ
- Details
Arba Minch University (AMU) hosted its 13th Annual Research and Publication Review Workshop, a two-day event held from February 6–7, 2026, at the Main Campus, during which key findings from 128 completed and 53 ongoing research projects were presented and constructive feedbacks from stakeholders were gathered. Click here to see more photos.





