አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የማካካሻ ትምህርት/Remedial / ፕሮግራም ለመከታተል ያለፉትን ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በግል ከፍሎ ለመማር የሚፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

Arba Minch University along with United Nations Industrial Development Organization has organized a half day capacity development and community engagement workshop to promote Moringa products in Ethiopia on October 20, 2023. Click here to see more photos.

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ /ICT/ ዳይሬክቶሬት በሥራ ክፍሉ ለሚገኙ ከየካምፓሱ ለተወጣጡ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ ጀማሪ ባለሙያዎች  በኮምፒውተር ማሽን ጥገና  እና በሲስተም ዴቨሎፕመንት አስተዳደር ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የግራንትና የትብብር ፕሮጀክቶች አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ለግብርና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን “Climate Risk Management in Agriculture” በሚል ፕሮጀክት ርዕሰ ጉዳይ ላይ መስከረም 29/2016 ዓ/ም ገለጻ ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የግራንትና የትብብር ፕሮጀክቶች አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ከውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሃይድሮሎጂና ሜትዎሮሎጂ ፋካልቲ ጋር በመተባበር ለፋካልቲው መምህራንና ለ3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች ከመስከረም 30 - ጥቅምት 01/2015 ዓ.ም ድረስ ለሁለት ቀናት የቆየ ሥልጠና ‹‹Satellite and Remote Sensing Applications›› በሚል ርዕስ ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ