አቶ አሰፋ ጨጉልኤ ከአባታቸው ከአቶ ጨጉልኤ ቂዳ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ሳባሬ ሳቂሞ በቀድሞ ጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር በቦንኬ ወረዳ በገረሴ ከተማ በ1966 ዓ/ም ተወለዱ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒቲ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 12ኛ ክፍል ተማሪ የአብሥራ ፍፁምና ዳግም ሰለሞን የጋሞ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ከሰኔ 10 – 15/2016 ዓ/ም ባዘጋጀው ዞናዊ የሳይንስና ፈጠራ ሥራዎች ኤግዚቢሽን ላይ የፈጠራ ሥራዎችን በማቅረብ ላደረጉት የላቀ ተሳትፎ ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና ኮሚዩኒቲ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዕውቅናና የተሳትፎ ምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ተመራቂ ተማሪዎች ተመርቀው በሚሄዱበት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገጥሟቸውን አዲስ የሥራ አካባቢዎችና የሚሰጣቸውን ኃላፊነት በጥንቃቄ በመቀበል የሚሰጧቸውን ማኅበራዊ አገልግሎቶች ሥነ ምግባራዊ እንዲያደርጉ በሥራ ሥነ ምግባር መርሆዎች እና በሙስና ወንጀል ሕጎች ዙሪያ ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና አዘጋጅቷል፡፡ ስለሆነም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ ከዚህ በታች በተያዘላችሁ ፕሮግራም መሠረት ሥልጠናውን እንድትካፈሉ እናሳስባለን፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስና ሥነሰብ ኮሌጅ በ«Geography and Environmental Studies» ትምህርት ክፍል በ«Environment and Natural Resource Management» ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር ዘውዴ ዓለማየሁ ሰኔ 21/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ ከ2፡30 ጀምሮ የ3ኛ ዲግሪ ማጠናቀቂያ ምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በዋናው ግቢ በድኅረ ምረቃ አዳራሽ ያቀርባል፡፡ ዕጩ ዶ/ር ዘውዴ ዓለማየሁ “LAND USE/LAND COVER CHANGE AND CLIMATE CHANGE: EFFECTS ON HYDROLOGICAL PROCESSES IN GILGEL GIBE CATCHMENT, ETHIOPIA” በሚል ርዕስ የመመረቂያ ጥናት ጽሁፍ አከናውኗል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ በእንስሳት ሳይንስ ት/ክፍል በ«Animal Production» ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር ሮባ ጂሶ ሰኔ 21/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ  የ3 ዲግሪ ማጠናቀቂያ ምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በዋናው ግቢ መግቢያ በር አከባቢ በሚገኘው አዳራሽ ያቀርባል፡፡ ዕጩ ዶ/ር ሮባ ጂሶ  “Feed resources Availability, Nutritional Quality, and Blood Biochemistry of Dromedary Camels (Camelus dromedarius) in Borana Plateau, Southern Ethiopia” በሚል ርዕስ  የመመረቂያ ጥናት ጽሁፉን አከናውኗል፡፡