Arba Minch University-Inter-University Cooperation Program Project III (P3) has conducted research dissemination and gap identification workshop on maternal and child health on April 19, 2023. Click here to see more pictures.

የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና አሠጣጥ እና የሪሜዲያል ተማሪዎች የማስተማር ሂደትን አስመልክቶ የተከናወኑ ተግባራት ያሉበት ሁኔታ እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ዲኖች፣ ሳይንቲፊክ ዳይሬክተሮች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎችና አስተባባሪዎች፣ ከየትምህርት ክፍሉ የተወጣጡ ተማሪዎችና የተማሪዎች ኅብረት ተወካዮች በተገኙበት ግምገማዊ የውይይት መድረክ ሚያዝያ 11/2015 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአየር ለውጥ ምክንያት በሚከሰት የድንች ምርት መቀነስ ዙሪያ የሚሠራ የ1.13 ሚሊየን ብር ግራንድ የምርምር ፕሮጀክት ሚያዝያ 11/2015 ዓ/ም ይፋ አድርጓል፡፡  ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲውና ለሀገራችን የእስልምና እምነት ተከታዮች እንዲሁም በመላው ዓለም ለምትገኙ የእምነቱ ተከታይ የሆናችሁ የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ምሩቃን (አሉምናይ) እንኳን ለ1444ኛው ኢድ አል-ፈጥር (የረመዳን ጾም ፍቺ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆን ከወዲሁ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የግራንትና ኮላቦሬቲቭ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት የምርምርና የትብብር ፕሮጀክቶች ግምገማ ሚያዝያ 10/2015 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡