የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማዕከል ‹‹የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አሠራር፣ የሚዲያ አተገባበርና ንቃት›› በሚል ርዕስ ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መጋቢት 30/2015 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የ1ኛ ዓመት ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ ኮሌጁን መርጠው አዲስ ለተቀላቀሉ የ2 ዓመት ተማሪዎች የእንኳን ደኅና መጣችሁ አቀባበል እንዲሁም በ2014 ዓ/ም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የ 3 እና የ4 ዓመት ተማሪዎች የሽልማት መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በግብርና ሳይንስ ኮሌጅ በእንስሳት ሳይንስ ት/ክፍል በእንስሳት ስነ-ምግብ ‹‹Animal Nutrition›› ትምህርት ፕሮግራም ላለፉት 6 ዓመታት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ጌታቸው አብርሃም የምርምር ሥራውን መጋቢት 28/2015 ዓ/ም የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርቦ ተገምግሟል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነትን አግኝቷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግሥት መስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ጋር በመተባበር በጎፋ ዞን መሎኮዛ ወረዳ በጫልቆ ወንዝ ላይ የሚገነባውን የጫልቆ ግድብና መካከለኛ የመስኖ ጥናትና ዲዛይን ንድፍ ሪፖርት ግምገማ ከመጋቢት 26 - 27/2015 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ