Oxford Brookes University, UK Centre for Development and Emergency Practices (CENDEP) Closed Call for Application for full funded Ph.D., Studentship From the Faculty Members of Arba Minch University; DETAILS OF ADVERTISEMENT

 

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ  ለዩኒቨርሲቲውና ለመላው የሀገራችን የክርስትና እምነት ተከታዮች  እንኳን ለብርሃነ ትንሣዔው በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆን  ከወዲሁ መልካም ምኞቱን  ይገልፃል!!

መልካም የፋሲካ በዓል! ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ማኅበረሰብ ጉድ/ማስ/ጽ/ቤት ከጋሞ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር በዳራማሎ ወረዳ ለዋጫ ከተማ ወጣት አደረጃጀት፣ ኢንተርፕራይዝ አካላትና ከመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ለተወጣጡ አካላት በአመራርነት፣ በሥራ ፈጠራ አመለካከትና የስኬታማ ሥራ ፈጣሪዎች መለያ ባህሪያት ዙሪያ ያተኮረ ሥልጠና ሚያዝያ 03/2015 ዓ.ም ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የብዝኃ ሕይወት ምርምርና ጥበቃ ማዕከል የእንሰት አጠውልግ በሽታ ስርጭትን ለመቀነስና ከበሽታው የጸዱ የእንሰት ዝርያዎችን አባዝቶ የማሰራጨት ተግባራትን የሚያከናውን ግራንድ የምርምር ፕሮጀክት ቀርጾ በጋሞና ጎፋ ዞኖች በሚገኙ አምስት ወረዳዎች ተግባራዊ እያደረገ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም እና ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የመጀመሪያውን የእንሰት መፋቂያ፣ መቁረጫ፣ መፍጫና መጭመቂያ ማዕከል በጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ዶርዜ ሆሎኦ ቀበሌ አቋቁሟል፡፡ በዚህም የአካባቢው እንሰት አብቃይ ሴት አርሶ አደሮች እንሰት ወደ ማዕከሉ በማምጣት በቴክኖሎጂው በመገልገል ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ