የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሙያ ማበልጸጊያ ማዕከል ከደረጃ ዶት ኮምና ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባባር ‹‹Arba Minch Job Fair›› በሚል ርእስ የመጀመሪያውን የሥራ ዐውደ ርእይ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መጋቢት 14/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከኢፌዲሪ የከተማና መሠረት ልማት ሚኒስቴር የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ጋር ሀገር አቀፍ የውኃ ዘርፍ የኮንስትራክሽን ሥራዎች የሰው ኃይልና የማሽነሪዎች ምርታማነት ኖርም (Standard Productivity Norm) ላይ በጋራ ለመሥራት መጋቢት 12/2016 ዓ/ም የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Arba Minch Institute of Technology/AMiT/ of Arba Minch University/AMU/ and Malta College of Arts Sciences and Technology/MCAST/ have inked a Memorandum of Understanding to establish a collaborative partnership aimed at enhancing student exchange, upgrading teaching standards, and promoting academic and cultural development on March 12, 2024, at Addis Ababa Sky-light Hotel, Ethiopia. The agreement outlined various areas of cooperation between the two institutions.

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጀርመን ተራድኦ ድርጅት/GIZ/ ጋር በመተባበር ለ“Forest for Future” ፕሮጀክት ግብዓት የሚሆን በ“Geographic Information System/GIS” እና በ“Global Positioning System/GPS”  ዙሪያ  ከገረሴ እና ምዕራብ አባያ ወረዳ ለመጡ 22 የደን እና የተፈጥሮ ሀብት አስተዳደር ባለሙያዎች ከመጋቢት 9 - 13/2016 ዓ/ም ድረስ ለተከታታይ 5 ቀናት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ትምህርትና ሥነ ባሕርይ ት/ቤት ከጫሞ ካምፓስ የፀረ-ኤች አይ ቪ/ኤድስና ሥነ ተዋልዶ ጤና ማስተባበሪያ ጋር በመተባበር ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ የልባም ሴት የስኬት ምሥጢር፣ የጾታዊ ጥቃት ምንነት እና ተያያዥ ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ መጋቢት 07/2016 ዓ/ም የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡