በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በባዮሎጂ ት/ክፍል በ"Biodiversity Conservation and Management" ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ማቲዎስ አጊዜ የምርምር ሥራውን ነሐሴ 29/2015 ዓ/ም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የፌዴራል ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለሥልጣን የፌዴራል የመንግሥት ተቋማትን የግዥ ሥርዓት ለማሻሻልና ለማዘመን  በ“Electronic Government Procurement /eGP” ዙሪያ ለዘርፉ የዩኒቨርሲቲው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በቲዎሪና በተግባር የተደገፈ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ከጳጉሜ 2-4 /2015 ዓ.ም ድረስ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በባዮሎጂ ት/ክፍል በ‹‹Biotechnology›› ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር ሳምሶን ትዕዛዙ  መስከረም 04/2016 ዓ/ም ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ  የ3 ዲግሪ ማጠናቀቂያ ምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በዓባያ ካምፓስ በአዲሱ ማኔጅመንት ሕንፃ አዳራሽ ያቀርባል፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከጃፓን አለምአቀፍ የትስስር ኤጀንሲ (JICA) ጋር በመሆን በግብርና፣ በትምህርት፣በፋይናንስ፣ በዲጂታል አይሲቲና በቱሪዝም ቴክኖሎጂዎች ማኑፋክቸሪንግ እና ማአድን የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በማወዳደር ፈጠራቸውን ለማሳደግ የሚረዳቸው የአቅም ግንባታ ስልጠና ለአራት ቀናት አመቻችተዋል፡፡ 

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከግብርና ሚኒስቴር፣ ከባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩትና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር ‹‹ወደ ዓለም አቀፍ የተመጣጠነ ምግብ ደኅንነት/Towards Global Food and Nutrition Security›› በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የእንሰት ሲምፖዚዬም ከጳጉሜ 1-2/2015 ዓ/ም የተለያዩ መርሃ ግብሮችን በማከናወን ተጠናቋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡