
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ከተባበሩት መንግሥታት የመድኃኒትና የወንጀል ጽ/ቤት በተገኘ ሰባ ዘጠኝ ሺህ አምስት መቶ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓትን ለማሻሻል እንዲሁም የፍትሕና የነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሳደግ ያለመ የትብብር ፕሮጀክት ሚያዝያ 25/2017 ዓ/ም ይፋ አድርጓል፡፡ ፕሮጀክቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ ስምንት ዞኖች ተግባራዊ የሚሆን ነው፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የሕግ ት/ቤት ከተባበሩት መንግሥታት የመድኃኒትና የወንጀል ጽ/ቤት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ተግባራዊ የሚሆን ፕሮጀክት ይፋ አደረገ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳዮች አካትቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ከኢትዮ ቴሌኮም ደቡብና ደቡብ ምዕራብ ሪጂን ጋር በመተባበር ለኢትዮ ቴሌኮም አምባሳደር ተማሪዎች እና ለእናት መቀነት ተጠቃሚዎች በኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎትና በሥሩ የሚገኙ የተለያዩ ሥራዎችን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሚያዝያ 25/2017 ዓ/ም ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በመጪው ግንቦት ወር ላይ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሚካሄደውን የውኃና ሃይድሮ ዲፕሎማሲ ፎረም አስመልክቶ በሚካሄደው የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የጥያቄና መልስ ወድድር ላይ ለሚሳተፉ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተማሪዎች ሚያዝያ 25/2017 ዓ/ም ወድድሩን አስመልክቶ ገለጻ ተሰጥቷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት ‹‹AMU Tech HUB›› የተሰኘ የተማሪዎች ክበብ ምሥርታ መርሃ ግብር ሚያዝያ 8/2017 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
AMU, Ayuda en AcciÓn, Qomar Spanish Food Company and Madrid Polytechnic University kicked off a new project entitled “Innovation in the Development of the Moringa Market system (INNMORE)” at Tourist hotel, Arba Minch, Ethiopia, on 13th May, 2025. The project fund was donated by Spanish Cooperation and Arba Minch University (AMU) involves as a lead partner whereas the local cooperative partners from Wolaita and Gamo Zones will be the project focus areas. AMU officials, project team members from Addis Ababa and Wolaita, higher officials and different sector leaders from Gamo and Wolaita zones, community members from the two zones cooperatives and private sectors invited participants graced the event. Click here to see more photos.