ረ/ፕ አባይነህ ኡናሾ ከአባታቸው ከአቶ ኡናሾ ጋንዲሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ፋስቴ ጡኖ በቀድሞው ጋሞ ጎፋ ጠቅላይ ግዛት ጋርዱላ አውራጃ ዘይሴ አካባቢ በ1950 ዓ/ም ተወለዱ፡፡

ረ/ፕ ጊሹ ሰሙ ከአባታቸው አቶ ሰሙ ተሊላ እና ከእናታቸው ወ/ሮ የሺ ኡርጌ ሰኔ 12/1968 ዓ/ም በቀድሞው አርሲ ክፍለ ሀገር በአርባ ጉጉ አውራጃ ልዩ ስፍራው ጮሌ በምትባል ቦታ ተወለዱ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሰሜኑ የሀገራችን አካባቢዎች በተከሰተው ጦርነት ሳቢያ ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ወገኖች የቁሳቁስና የምግብ ጥሬ ዕቃዎችን እንዲሁም ለአገር መከላከያ ሠራዊት የገንዘብና የደም ልገሳ ድጋፎችን እያካሄደ ይገኛል፡፡ 

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባህልና ቋንቋ ጥናት ኢንስቲትዩት በዘርፉ የሚከናወኑ የጥናትና ምርምር ንድፈ ሃሳቦች የ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር ግምገማ መስከረም 8/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ለግምገማ የቀረቡት 30 የምርምር ንድፈ ሃሳቦች ሲሆኑ አብዛኛዎቹ በሀገረሰብ ዕውቀቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 1 የ3ኛ ዲግሪና 7 የ2ኛ ዲግሪ ትምህርት ፕሮግራሞችን ለመክፈት የሚያስችለውን የውጭ ሥርዓተ-ትምህርት ግምገማ የዘርፉ ምሁራን በተገኙበት ከመስከረም 6 - 7/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ