የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ- ትምህርትና  ሥነ-ባህርይ ሳይንስ ትምህርት ቤት የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል 2 አመት ተማሪ የሆነው ናትናኤል ፀጉ አሰፋ  ከጓደኛው ጋር በተፈጠረ የግል ፀብ በደረሰበት ጥቃት ዛሬ ጠዋት ሚያዚያ  28 ቀን 2017 /   ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል:: በመሆኑም ሕይወቱን ለማትረፍ በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ ርብርብ ቢደረግም ሳይሳካ በመቅረቱ ማምሻውን 12:30 ላይ ሕይወቱ አልፏል። 

ጥቃቱን ያደረሰው ተማሪ በቁጥጥር ስር ውሎ አስፈላጊው ምርመራ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው የሕግ ሂደቱን በመከታተል  ውሳኔውን ተከታትሎ በአጭር ጊዜ ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል::

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተማሪ ናትናኤል ከዚህ አለም በሞት መለየት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ሁሉ መፅናናትን ይመኛል።

ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-

ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/

ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university

ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityccd/

ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA

የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት