/ መቅደስ ኃይሉ ከአባታቸው አቶ ኃይሉ ሐጎስ እና ከእናታቸው / ገነት ክበበው ጥቅምት 2/1968 / በአዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ፡፡ 

 

የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ 1 እና መለስተኛ 2 ደረጃ /ቤት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ አጠቃላይ 2 ደረጃ /ቤት ተከታትለዋል፡፡ / መቅደስ ከአርባ ምንጭ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ 10+2 በሴክሪተያል ሳይንስ ታህሳስ 30/2001 / የተመረቁ ሲሆን ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ሰኔ 26/2006 / በማኔጅመንት የትምህርት ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡

 

/ መቅደስ ኃይሉ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን ከተቀላቀሉበት ከታህሳስ 20/1993 / ጀምሮ ዩኒቨርሲቲውን በተለያዩ የሥራ መደቦች ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ለረጅም ዓመታት አገልግለዋል፡፡  

 

/ መቅደስ ኃይሉ በዩኒቨርሲቲው የብቃትና ሰው ኃብት ሥራ አስፈጻሚ /ቤት ሥር የሰው ሀብት አስተዳደር ቡድን መሪ በመሆን ሕይወታቸው አስካለፈበት ዕለት ድረስ በታማኝነትና በቅንነት ተቋሙን ሲያገለገሉ ቆይተዋል፡፡

 

 / መቅደስ ኃይሉ በተወለዱ 50 ዓመታቸው መስከረም 18/2018 / በድንገተኛ ሕመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

 

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በወ/ መቅደስ ኃይሉ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ ለሟች ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣ የሥራ ባለደረቦች እንዲሁም ለመላው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ መጽናናትን ይመኛል፡፡

 

 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ