አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለአዲስ ገቢና ለሪሚዲያል ተማሪዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የኤሌክትሮኒክ የትምህርት አሰጣጥን ለማጠናከር የሚረዳ ኦንላይን ኮርስ ለማስጀመር /E-LEARNING FOR STRENGTHING HIGHER EDUCATION (E-SHE)/ በሚል ርእስ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ትግበራና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ሰረቀብርሃን ታከለ መርሃ ግብሩ ዲጂታል ሊትረሲን የተመለከተ መሆኑን ገልጸው ይህም በሀገር ደረጃ በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ለመተግበር የተያዘ ዕቅድ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች በቀጣይ ሴሚስቴር ኦንላይን የሚሰጡ ኮርሶች እንዳሉ የገለጹት ዳይሬክተሩ የግንዛቤ ማስጨበጫው ለዚያ ብቁ  እንዲሆኑ እንደሚረዳቸውም ተናግረዋል፡፡ 

የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንትፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሉነህ ለማ ሥልጠናው ቴክኖሎጂን በመጠቀም ትምህርትን ለማዘመን እንዲሁም ከዲጂታል ሊትረሲ ጋር በተያያዘ አዲስ ተማሪዎች ለተለያዩ መጭበርበሮች እንዳይጋለጡና ትክክለኛ መረጃን መለየት ላይ ያላቸውን ክፍተት ለመሙላት የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የe-learning አስተዳደር ዩኒት ዳይሬክተር ዶ/ር መሐመድ አበበ በበኩላቸው የሪሚዲያል እና አዲስ ገቢ ተማሪዎች በኦንላይን ለሚሰጡ ኮርሶች የሚጠቅማቸውን ሥልጠናዎች የትና እንዴት ማግኘት እንደሚችሉና ጠቀሜታቸው ላይ ማብራሪያ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል፡፡ ሂሳብና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኦንላይን ከሚሰጡ ኮርሶች ተጠቃሽ ናቸው ያሉት ዳይሬክተሩ ፕሮጀክቱ በትምህርት ሚኒስቴር የሚመራ የአምስት ዓመት ፕሮጀክት መሆኑንና የተለያዩ አጋዥ አጋር ድርጅቶች በሥራው እንደሚሳተፉ ተናግረዋል፡፡ ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በተቋሙ ባሉ ቤተሙከራዎች በሚሰጣቸው አካውንቶች እየገቡ ኮርሱን መከታተል እንደሚጀምሩና የአይሲቲ ባለሙያዎች ድጋፍ እንደሚደርጉላቸው ዶ/ር መሐመድ ጠቁመዋል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!

ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-

ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/

ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university

ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityccd/

ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA

የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት