ዓለም አቀፍ የኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንት ከኅዳር 9 - 15/2017 በመላው ዓለም ይከበራል። ይህን ታሳቢ በማድረግ የአምዩ የሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልፀጊያ ማዕከል በተማሪዎች መካከል የቢዝነስ ሃሳብ ውድድር አዘጋጅቷል።

ስለሆነም የቢዝነስ ሃሳብ ያላችሁ ተማሪዎች ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (Link) https://forms.gle/ayoEzKtEYfWHQ35MA በመጫን እንድትመዘገቡ እየጋበዘን ሃሳባችሁን በግልም ሆነ በቡድን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ለአሸናፊዎች የማበረታቻ ገንዘብ እና የምስክር ወረቀት የምንሸልም መሆኑንም እናሳውቃለን፡፡ 

ማሳሰቢያ፡
•    የምትወዳደሩበት የቢዝነስ ሃሳብ ከዚህ በፊት ተወዳድራችሁበት ሽልማት ያገኛችሁበት መሆን የለበትም
•    ውድድሩ አሁን በትምህርት ላይ ያሉ ተማሪዎችን ብቻ የሚመለከት ይሆናል
•    የምዝገባ ጊዜ ከጥቅምት 28/2017 እስከ ኅዳር 5/2017 ዓ.ም ነው

የአምዩ የሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልፀጊያ ማዕከል

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!

ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-

ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/

ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university

ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityCAD/

ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA

የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት