በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአገራዊ የድህረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና (National Graduate Admission Test - NGAT) ለመፈተን የተመዘገባችሁ ተፈታኞች በሙሉ፣ ፈተናውን በተመለከተ የሚከተሉትን አስፈላጊ መረጃዎች በጥንቃቄ እንድትመለከቱ እናሳስባለን።
1. የቀን፣ የሰዓትና የፈተና ቦታ መረጃ
- የፈተና ክፍል ማወቂያ ዝርዝር፦ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም. ከቀኑ 2፡30 ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ዋና መግቢያ በር ላይ ይለጠፋል።
- የፈተና መስጫ ቦታ፦ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ
- የፈተና ቀን፦ ረቡዕ፣ ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም. እና ሐሙስ ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም
- የፈተና መጀመሪያ ሰዓት፦ ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ
2. ማሳሰቢያ
- የፈተና መግቢያ ካርድ፦ የፈተና መግቢያ ካርድ ከሲስተሙ ማውረድ ስለተፈቀደ፣ በተመዘገባችሁበት የግል አካውንት በመግባት የፈተና መግቢያ ካርዳችሁን ማውረድና ይዛችሁ መምጣት አለባችሁ።
- ሕጋዊ መታወቂያ፦ ለፈተና ስትመጡ ማንነታችሁን የሚያረጋግጥ ሕጋዊ መታወቂያ ወይም ፋይዳ መታወቂያ (Fayda ID) ይዛችሁ መገኘት አለባችሁ።
- የተከለከሉ ዕቃዎች፦ ወደ ፈተና ጣቢያ ሞባይል ስልክ፣ ሳይንቲፊክ ካልኩሌተር እና ሌሎች የተከለከሉ ዕቃዎችን ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
ድኅረ-ምረቃ ት/ቤት

