በ2017 የትምህርት ዘመን አዲስ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ቅበላ ረቡዕ ታኅሣሥ 2 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ምዝገባ ሐሙስና ዓርብ ታኅሣሥ 3 እና 4 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ትምህርት የሚጀመረው ሰኞ ታኅሣሥ 7 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል፡፡
በዚህ መሠረት የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው አባያ ካምፓስ፣
የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ A እስከ R የሆናችሁ የማኅበራዊ ሳይንስ (Social Science) የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው ጫሞ ካምፓስ፣
እንዲሁም የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ S እስከ Z የሆናችሁ የማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በሚገኘው ሳውላ ካምፓስ ሬጅስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች በአካል እየቀረባችሁ በተጠቀሰው ቀን ሪፖርት እንድታደርጉ፣ ምዝገባ እንድትፈጽሙ እና ትምህርት እንድትጀምሩ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
1ኛ) ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕትና የ12ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ኦርጂናልና የማይመለስ ሁለት ኮፒ እንዲሁም አንሶላ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ በመያዝ መምጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡
2ኛ) ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው አያስተናግድም፡፡፡
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityCCD/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA
የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት