OFAB (Open Forum for Agricultural Biotechnology) አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን የSouth Node ማዕከል አድርጎ በመምረጥ የምስረታ አውደ ጥናቱን ጥር 07/2008 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ Click here to see the Pictures.

የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ማህበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከኮምፒውተር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር ከአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው 2ኛ ደ/መ/ት/ቤቶች ለተወጣጡ 95 መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች ከታህሳስ 23 - ጥር 21/2008 ዓ/ም ለተከታታይ አራት ቅዳሜዎች መሠረታዊ የኮምፒውተር ክህሎት ስልጠና ሰጥቷል፡፡ Click here to see the Pictures.

ከኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ማኅበር እና ከ CDC/Center for Disease Control and Prevention/ ጋር በመተባበር የሚሠራው የአርባ ምንጭ ሥነ-ህዝብና ጤና ልማት ማዕከል በ2008 ዓ.ም የሀገር ዓቀፉ INDEPTH አባል ሆኗል፡፡

ምርምር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካስቀመጧቸው የትኩረት መስኮች አንዱና መሰረታዊ እንደመሆኑ መጠን ተቋሙንና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲሁም በገበያ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት የሚያስችል ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲው የሚሰጣቸውን አገልግሎቶችና የአገልግሎት አሰጣጥ መስፈርቱን እንዲሁም አገልግሎቱ የሚሰጥበትን ቦታና ደንበኞች አገልግሎት ለማግኘት በቅድሚያ ማሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታ በዝርዝር ለተገልጋዮች ለማሳወቅ የዜጎች ቻርተር አዘጋጅቷል፡፡