
- Details
የደቡብ ኢትዮጵያ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ባዘጋጀው የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ላይ የተወዳደሩት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ብዝኀ ሕይወት ምርምርና ጥበቃ ማእከል ተመራማሪ አታላይ አዘነ ውድድሩን በሦስተኛነት በማጠናቀቅ የሰርተፊኬትና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝደንቶች፣ ሌሎች የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተወካዮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የኢትዮጵያ ምርምር ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመሥርቷል።ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት የ2017 ዓ/ም ትምህርት ዘመን ማጠናቀቂያ፣ የቅድመ መደበኛ ተማሪዎች ምረቃ፣ የተማሪ ወላጆች ቀንና የውጤት ማሳወቂያ መርሐ ግብር ሐምሌ 12/2017 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት የ2017 ዓ/ም ትምህርት ዘመን ማጠናቀቂያ የወላጆች ቀንና የቅድመ መደበኛ ተማሪዎች ምረቃ በዓል ተከበረ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በሥሩ ከሚገኙ የሥራ ክፍሎች ጋር ሐምሌ 9/2017 ዓ/ም በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል።ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: ኮሌጁ በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄደ
- Details
የፊታችን ሐሙስ ሐምሌ 24/2017 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እንደሚካሄድ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ በዚህ ሀገራዊ መርሐ ግብር ላይ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግ እያሳሰብን በዕለቱ የሚኖረው መርሐ ግብር እንደሚከተለው ይሆናል፡፡
1.የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላትና ከፍተኛ አመራሮች በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ በላንቴ ቀበሌ የችግኝ ተከላውን የሚያከናውኑ ይሁናል፡፡
2.መላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ በየካምፓሱ ለተከላው በተዘጋጁ ቦታዎች የችግኝ ተከላውን የሚያከናውኑ ይሆናል፡፡