
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲሱን ዓመት በማስመልከት ለአረጋውያን፣ ለአቅመ ደካሞች፣ በተለያዩ ምክንያቶች ወላጆቻቸውን ላጡና ለዘማች ቤተሰብ አባላት በድምሩ ለ115 አባወራዎች ለእያንዳንዳቸው 25 ኪሎ ግራም በድምሩ 29 ኩንታል የሚሆን የፉርኖ ዱቄት ለማዕድ ማጋራት እንዲውል ለአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ 03/2014 ዓ/ም አስረክቧል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን 150 ሺ ብር የሚጠጋ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ክርስቲያን ኤይድ/Christian Aid/ ከተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በካምባ ወረዳ ዲንጋሞ ቀበሌ ማይጸሌ ወንዝ ላይ የሚያስገነባው አነስተኛ የውሃ ኃይል ማመንጫ የዲዛይንና ቅድመ ጥናት ሥራ ዙሪያ የክርስቲያን ኤይድ ኢትዮጵያ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፕሮጀክቱ አባላትና አማካሪ ቦርድ አባላት በተገኙበት ነሐሴ 25/2014 ዓ/ም ውይይት ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት የማኅበረሰብ ጉድኝት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን/The United Nations High Commissioner for Refugees (UNHCR) ቢሮ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በተፈናቃይ ሰዎች የሕግ ጥበቃ፣ በሴቶችና ሕፃናት መብት ጥበቃ፣ በንብረት ሕግ እንዲሁም በካምፓላ ስምምነት ዙሪያ በአሌ ልዩ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ 17 ቀበሌያት ለተወጣጡ የማኅበራዊ፣ የወረዳና የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች፣ መርማሪ ፖሊሶች፣ የፍትሕ ቢሮ ዐቃቤያን ሕግ እንዲሁም ከሴቶችና ሕፃናት እና ከልዩ ወረዳው ምክር ቤት ለተወጣጡ 30 ሠልጣኞች ከነሐሴ 30 - ጳጉሜ 1/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በሴቶችና ሕፃናት መብት ጥበቃ እና በንብረት አያያዝና አስተዳደር ላይ ያተኮረ የሕግ ግንዛቤ ማጎልበቻ ሥልጠና ተሰጠ