Arba Minch University in association with the House of Federation and Ministry of Education will celebrate 10th Ethiopian Nations, Nationalities and People’s Day with great enthusiasm on 26th November, 2015, at Main Campus. 

ዩኒቨርሲቲው በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን የአከዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚደንት ቢሮ እና የሥርዓተ-ፆታ ዳይሬክቶሬት ገልፀዋል፡፡

በትምህርት ተቋማትና በሴክተር መስሪያ ቤቶች አመራር የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ መንግስት በያዘው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሰረት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 7 % የነበረውን የሴት መምህራን ቁጥር በ5 ዓመት ውስጥ ወደ 36% ለማሳደግ ዕቅድ ይዟል ፡፡በዚህም መሰረት በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ውሳኔ በ2007 /ም ከየትምህርት ክፍሉ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የተመረቁ 34 ሴት ተማሪዎችን በዩኒቨርሲቲው በመምህርነት በመቅጠር ዕቅዱን ለማሳካት እየሠራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ደርዛ ገልፀዋል ፡፡

የዩኒቨርሲቲው የስርዓተ ፆታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሪት ሙኒት መኩሪያ በበኩላቸው መምህራኑ በቅድሚያ የህይወት ክህሎት ፣ የጥናትና ምርምር ስነ-ዘዴ፣ የስርዓተ ፆታ ምንነትና ፅንሰ ሃሳብ ስልጠና እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል ፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ በርካታ ሴት መምህራንን መቅጠር የተፈለገው በዩኒቨርሲቲው በመምህርነትና በአመራር ላይ በቂ ሴቶች ባለመኖራቸውና በቀጣይም የሴቶችን የውሳኔ ሰጪነት ሚና ለማሳደግ ብሎም ሴት ተማሪዎችን እንዲያበረታቱ ለማድረግ ነው ፡፡በመሆኑም አዲስ ተቀጣሪ መምህራን ጠንክረው እንዲሰሩና ለሌሎችም ተምሳሌት እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡

አካዳሚው ከሚያከናውናቸው አበይት ተግባራት መካከል የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስፖርት ፌስቲቫል መሳተፍ፣ የስፖርት ማዘውተሪያዎችን መገንባትና ማደስ፣ የተለያዩ ስልጠናዎችን መስጠትና ዓመታዊ የጥናትና ምርምር አውደ ጥናት ማካሄድ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የአካዳሚው ዳይሬክተር ዶ/ር ቾምቤ አናጋው እንደገለፁት በ2008 በጀት ዓመት በጅማ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል ዩኒቨርሲቲውን ወክለው የሚሳተፉ ስፖርተኞችን ለመመልመል የሚያስችል የውስጥ ውድድር እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በየካምፓሱ በሚደረጉ የተለያዩ ውድድሮች ዲፓርትመንቶች ለካምፓስ ዋንጫ የሚፎካከሩ ሲሆን በውድድሩ የተሻለ ብቃት ያላቸው ስፖርተኞች ዩኒቨርሲቲውን በመወከል በስፖርት ፌስቲቫሉ ይሳተፋሉ፡፡ዩኒቨርሲቲው ለመጀመሪያ ጊዜ የባህል ስፖርትን ጨምሮ በ13 የስፖርት ዓይነቶች ይወዳደራል፡፡
አካዳሚው የስፖርት ማዘውተሪያዎችን በመገንባትና በማደስ ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ እየሠራ ይገኛል፡፡ በነጭ ሳርና በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ካምፓሶች የጂምናዚየም አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን በቅርቡ የውሃ ዋና አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡  በሌሎች ካምፓሶችም ተጨማሪ ጂምናዚየሞች እንደሚገነቡ ተገልጿል፡፡
አካዳሚው ለስፖርተኞችና በዞኑ ለሚገኙ የስፖርት ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለመስጠትም አቅዷል፡፡ በዚህም መሠረት ለተመረጡ ከ15 ዓመት በታች ለሆኑ ለ30 ወንድና ለ30 ሴት ታዳጊ ሕፃናት የእግር ኳስ እንዲሁም ለተመረጡ ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ 10 ወጣቶች የአትሌቲክስ ሥልጠና ይሰጣል፡፡ በተጨማሪም ለስፖርት ሳይንስ ተማሪዎች በተመረጡ የሙያ ዘርፎች ባለሙያዎችን ከውጪ በመጋበዝ ተጨማሪ ዕውቀት የሚያገኙበት ስልጠና የሚሰጥ ሲሆን በእግር ኳስ ዳኝነትና አሰልጣኝነት ከ5ቱም ካምፓሶችና ከአካባቢው የሚመረጡ ተማሪዎች ስልጠና ያገኛሉ፡፡ የቴክኖሎጂና ዕውቀት ሽግግር ለመፍጠር ዓመታዊ የጥናትና ምርምር አውደ ጥናት ማካሄድም በዕቅዱ ተካቷል፡፡

Arba Minch University, with various reforms in academic and administrative arenas, is moving in right track to address institutional issues that invariably complement national needs. President, Dr Feleke Woldeyes, speaking on the broad spectrum of interests revealed as to how they will transform university in totality.