• SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • AMU
    • About AMU
    • Presidents Message
    • Campus Guide
    • Contact us
  • Administration
    • Presidents' Office
      • AMU President
      • Academic Affairs
      • Research and Community Service
      • Administration
  • Directorates
  • Academics
    • School of Graduate Studies
    • Institutes
      • Arba Minch Institute of Technology
      • Arba Minch Water Technology
    • Colleges
      • Agriculture
      • Business & Economics
      • Medicine and Health Sciences
      • Natural & Computational Sciences
      • Social Sciences & Humanities
      • Continuing & Distance Education
      • Sawla Campus
    • Schools
      • School of Law
      • School of Pedagogical and Behavioral Sciences
      • School of Medicine
    • Sport Academy
  • Research
  • Registrar
    • About Us
    • Alumni Registration
    • Alumni
  • Partnership
    • Our Partners
      • International Partners
      • Local Partners
    • Ongoing Projects
    • Completed Projectss
      • Recently Completed
      • Past Projects
    • GCPM Online Forms
  • Journals
    • OMOIJS Journal
    • EJBSS Journal
    • EJWST Journal
    • AMUJCLS Journal
    • EIJET journal
  • Symposia
    • Enset Symposium
    • Enset Symposium 2024
photo_2024-02-21_10-01-18.jpeg
photo_2025-05-06_09-54-21.jpeg
photo_2025-05-06_09-54-38.jpeg
1.jpeg
2.jpeg
previous arrow
next arrow

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አራተኛ አመት ክብረ በአል በድምቀት ተከበረ

Details
Thu, 23 July 2015 11:10 am

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ የተጣለበትን አራተኛ አመትና የግንባታውን መጋመስ በማስመልከት መጋቢት 29/2007 ዓ/ም ዩኒቨርሲቲው ዕለቱን በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል፡፡

የግድቡ ግንባታ ኃይል ከማመንጨት ዓብይ ዓላማው ባሻገር ተምሳሌታዊ የሆነ ጠቀሜታ ያለውና የአይቻልም መንፈስን ሰብሮ ወደ ይቻላል መንፈስ ያሸጋገረ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ገልፀዋል፡፡ እየተካሄደ ላለው የልማትና የዲሞክራሲ ሂደት በተለይም ለኢንዱስትሪው ሴክተር በቂ ኃይል በማቅረብ ልማታችንን የሚያፋጥን መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ አክለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ ከድህነት ለመውጣት እያሳየ ያለውን ጥረት ለማስቀጠል የህዳሴ ግድቡን ጨምሮ የተጀመሩ ልማቶችን ከግብ ለማድረስ ሁሉም ዜጋ በቁርጠኝነት መረባረብ አለበት ሲሉ የዩኒቨርሲቲው ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍስሃ በቀለ አስገንዝበዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከምስረታው ጊዜ ጀምሮ የአገራችንን የውሃ ኃብት ለማበልፀግ ታስቦ የተቋቋመ እንደመሆኑ በዘርፉ የሠለጠኑ ምሁራንን ለአገር በማበርከት ግንባር ቀደም ሚና መጫወት እንደሚጠበቅበት እሙን ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተቋሙ ሠራተኞች የሁለት ወር ደመወዛቸውን መቶ ፐርሰንት በመክፈል ቦንድ የገዙ ሲሆን ተማሪዎችም ከወር ቀለባቸው በመቀነስ ለግንባታው ስኬት ድጋፍ አድርገዋል፡፡

‹‹አሻራችን ያረፈበት ነውና ኩራት ሊሰማን ይገባል!›› ያሉት የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት ነገ የተሻለች ሀገር እንድትኖረን ለማድረግ ሁሉም ዜጋ ለግድቡ ግንባታ ካለው ላይ በመቀነስ የሚደያደርገውን ድጋፍ ሳያቋርጥ መቀጠል አለበት በማለት አሳስበዋል፡፡

ፕሮግራሙ በተለያዩ የስነ-ጹሁፍ ስራዎች፣መዝሙሮች፣ስፖርታዊ ውድድሮችና በሌሎች አዝናኝ ትዕይንቶች ደምቆ የተከበረ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣የአስተዳደር ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች፣ ተማሪዎችና መምህራን ተሳትፈዋል፡፡

ለዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራር በኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ሜይንስትሪሚንግ ላይ ስልጠና ተሰጠ

Details
Thu, 23 July 2015 11:09 am

በዩኒቨርሲቲው የሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬት ለዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራርና ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተወጣጡ ኃላፊዎች ሰኔ 6/2007 ዓ/ም የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ሜይንስትሪሚንግ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የሥልጠናው ዋና ዓላማ በኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ሜይንስትሪሚንግ ላይ ግንዛቤ በማዳበርና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ በማሳደግ የጋራ መግባባት ማምጣት መሆኑን በዩኒቨርሲቲው የሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታደሰ ዓለሙ ገልጸዋል፡፡

በስልጠናው ‹‹የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት›› በሚል ርዕስ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን አቶ በኃይሉ መርደኪዮስ እንዲሁም በሜይንስትሪሚንግ ምንነትና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በአቶ አለሙ ጣሚሶ የተዘጋጁ የውይይት ሰነዶች ቀርበው ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

በቀረቡት የውይይት ሰነዶች መነሻነት ከተሳታፊዎች አስተያየቶችና ጥያቄዎች የተሰነዘሩ ሲሆኑ በባለሙያዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ መሰል ስልጠናዎችን በየደረጃው ባሉ እርከኖች በመስጠት ግንዛቤውን ማዳበር ይገባል ያሉት ተሳታፊዎቹ በዩኒቨርሲቲው በሚገኙ የሥራ ክፍሎች የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ጉዳይ የዕቅድ አካል ሆኖ የክትትልና ድጋፍ ሥርዓት መዘርጋት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ለኤች.አይ.ቪ/ኤድስ አጋላጭ የሆኑ የኢኮኖሚ ችግሮችን ከመቅረፍ አንጻር ሴት ተማሪዎችንና ሌሎችንም የመደገፍና የመንከባከብ ሥራ ሊታሰብበት ይገባል ብለዋል፡፡

በሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬት የኤች.አይ.ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ቡድን አማካኝነት በተሰጠው በዚህ ሥልጠና የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዝደንት ጨምሮ ከ40 የሚበልጡ የበላይ አመራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ የሥራና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡



“ምርምር ለልማት” በሚል መሪ ቃል ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር አውደ ጥናት ተካሄደ

Details
Thu, 23 July 2015 11:08 am

በማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ እንዲሁም በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጆች አዘጋጅነት ‹‹ምርምር ለልማት›› በሚል መሪ ቃል ከሚያዚያ 30-ግንቦት 1/2007 ዓ/ም ለ3ኛ ጊዜ በዋናው ግቢ በተካሄደው ሀገር አቀፍ የምርምር አውደ ጥናት ላይ ከ15 ዩኒቨርሲቲዎችና ምርምር ተቋማት በተወጣጡ ጥናት አቅራቢዎች 30 ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበዋል ፡፡

በዩኒቨርሲቲው የምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ፋንታሁን ወልደሰንበት እንደገለጹት አውደ ጥናቱ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ውስጥ የሚሠሩ ተመራማሪዎች በወቅታዊ ችግሮች ላይ የጋራ ግንዛቤ በመያዝ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን እንዲጠቁሙ የሚያግዝ ነው፡፡ በተጨማሪም ዓውደ ጥናቱ በዩኒቨርሲቲዎች መካከል የልምድ ልውውጥ በማድረግና የትብብር ምስረታዎችን በማጠናከር ረገድ ሀገራዊ ፋይዳው የጎላ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ጥናታዊ ጹሑፎቻቸውን ካቀረቡት መካከል በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሚዩኒኬሽን ትምህርት ክፍል መምህር ሙዑዝ ሃይሉ አንዱ ሲሆኑ የጥናታቸውም ርዕስ “ሀገር አቀፍና አለም አቀፍ ጋዜጦች ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሰጡት ሽፋን” የሚል ነው፡፡ መገናኛ ብዙሃን ከሚዲያ መርሆች አንፃር ግድቡን አስመልክቶ እንዴት እደዘገቡት ማወቅን ዓላማ ያደረገው ጥናት በአንዳንድ ጋዜጦች ላይ የሚወጡ ዘገባዎች የናይል ተፋሰስ አገሮችን ጥቅምና ፍላጎት ማዕከል ያደረጉ ሳይሆኑ በየአገሮቻቸው ፍላጎት ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸውን ያሳያል፡፡ ግድቡ ለኢትዮጵያም ሆነ ለጎረቤት ሀገሮች ያለው የልማት ጠቃሚነት የጎላ ስለሆነ ሚዲያዎች ሚዛናዊ ሽፋን መስጠት እንደሚገባቸው በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡

በዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ-ጽሑፍ (አማርኛ) ትምህርት ክፍል መምህርት ህሊና ሰብስበው ‹‹የግጭት አፈታት ሥርዓት ክዋኔ በጌዲኦ ብሄር›› በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረበች ሲሆን የብሄረሰቡ የግጭት አፈታት ሥርዓት ከማህበረሰቡ መልካም እሴቶች ጋር የተቆራኘ መሆኑን እና የማህበረሰቡን የእርስ በእርስ ግንኙነት እንደሚያጠናክር ዳስሳለች፡፡ የጥናት አቅራቢዋ በሰጠቸው ተጨማሪ አስተያየት በአውደጥናቱ የተለያዩ የምርምር ውጤቶች መቅረባቸው ወጣት ተመራማሪዎች ልምድ እንዲቀስሙ ያስችላል ብላለች፡፡

በዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ዩኒቨርሲቲው በዋናነት ከሚያሳካቸው አበይት ተልዕኮዎች መካከል ማህበረሰብ ተኮር የሆኑ ምርምሮች ማካሄድ አንዱ ስለሆነ ተመሳሳይ የምርምር ስራዎች በቀጣይም በሌሎች ኮሌጆች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አሳውቀዋል፡፡

 

የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ የ‘ISIS’ን የሽብር ጥቃት በጥብቅ አወገዘ

Details
Thu, 23 July 2015 11:04 am

የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ሚያዝያ 16/2007 ዓ.ም በሁሉም ካምፓሶች በተደረገው የጧፍ ማብራት ሥነ-ሥርዓት ላይ በመገኘት በሊቢያ በ30 ኢትዮጵያውያን ላይ ISIS በተባለ አሸባሪ ቡድን እንዲሁም በደቡብ አፍሪካ በ4 ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመውን ኢ-ሰብዓዊ ግድያ በጥብቅ አውግዟል፡፡

በዋናው ግቢ በህሊና ፀሎት የተጀመረውን ሥነ-ሥርዓት በከፈቱበት ወቅት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ እንደተናገሩት በሁለቱም ሀገራት በዜጎቻችን ላይ የተፈፀመው ኢ-ሰብዓዊና አሰቃቂ ግድያ የኢትዮጵያውያንን ልብ በሐዘን የሰበረና በከፍተኛ ሁኔታ ቁጣ የቀሰቀሰ ነው፡፡ ፕሬዝደንቱ የጥቃቱ ሰለባ ለሆኑት ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለመላው ኢትዮጵያውያን መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡ በተጨማሪም ሀገራችን ኢትዮጵያ የምታደርገው የዴሞክራሲ ግንባታና ልማት ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሸባሪዎች ዕኩይ ዓላማቸውን ለመፈፀም በሚያቀርቡት ሃይማኖታዊ ሽፋን ሳንደናገር የፀረ ሽብርተኝነት አቋማችን ምንግዜም የፀና መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚጠበቅብን አሳስበዋል፡፡

በሌሎቹም ግቢዎች የፕሬዝደንት ተወካዮች፣ የኮሌጅ ዲኖችና የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝደንት ተወካዮች ለተጎጂ ወገኖች የተሰማቸውን ሐዘን በመግለጽ መንግሥት ሽብርተኝነትን ለመከላከል በሚያደርገው እንቅስቃሴ ሁሉም ዜጋ ከጎን በመሆን የሚጠበቅበትን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

በተለይም የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝደንትና ተወካዮቹ በሀገራችን ሠርተን የመሻሻል አማራጮች በርካታ ስለሆኑ በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር በመውጣት የአሸባሪዎች ሲሣይ መሆን ሊያበቃ ይገባል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ሽብርተኝነትን ከመታገል ጎን ለጎን ወጣቶች በሀገር ውስጥ የተፈጠሩና እየተፈጠሩ ያሉ የሥራ አማራጮችን አሟጠው እንዲጠቀሙና በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር እንዳይወጡ ግንዛቤ ከማስጨበጥ አንፃር የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ግንባር ቀደም ሚና መጫወት እደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሽብር ድርጊቱን የሚያወግዙ የተለያዩ የሥነ-ጽሑፍ ዝግጅቶች ቀርበዋል፡፡ የሥነ-ሥርዓቱ ተካፋዮችም ‹‹አክራሪነትና ሽብርተኝነት የትኛውንም ኃይማኖት አይወክልም››፣ ‹‹አንድነታችንን አጠናክረን ሽብርተኝነትን እንዋጋለን››፣ ‹‹የአይኤስአይኤስ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊትን በጥብቅ እናወግዛለን›› የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን በመያዝና በጋራ ድምጽ በማሰማት ጧፍ እያበሩ በየግቢው በተዘጋጁ ቦታዎች የጥቃቱ ሰለባዎችን በማሰብ የእግር ጉዞ አድርገዋል::

ዩኒቨርሲቲ አቀፍ የትምህርት ጥራትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ማጎልበቻ ፎረም ውይይት ተካሄደ፡፡

Details
Thu, 23 July 2015 11:03 am

የፎረሙ ውይይት በዋናው ግቢ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ የኮሌጅ ዲኖች፣የአስተዳደር ሠራተኞች፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት ሚያዝያ 30 ተካሂዷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ኮንፈረንሱን በንግግር በከፈቱበት ወቅት መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ትግል የትምህርት ጥራትና የመልካም አስተዳደር ፎረም ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም የፎረሙ ተሳታፊዎች ከመልካም አስተዳደርና ከትምህርት ጥራት አንፃር መሻሻል የሚገባቸውን አፈጻጻሞች በተመለከተ የጋራ ግንዛቤ ለመያዝ በሚያስችል መልኩ ውይይቱን እንዲያካሂዱ አሳስበዋል፡፡

ኮንፈረንሱ በዩኒቨርሲቲው ቀደም ሲል በትምህርት ክፍሎችና በኮሌጆች ደረጃ በተከታታይ በተደረጉ ውይይቶች ተለይተው የወጡ ችግሮችንና ድክመቶችን እንደየባህሪያቸው የአጭር፣ የመካካለኛ እና የረዥም ጊዜ ዕቅድ በማውጣት በዘላቂነት ለመፍታት እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎችን አስመልክቶ የአስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ የሁሉንም ኮሌጆችና የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሪፖርት አቅርበዋል፡፡

ሪፖርቱን ተከትሎ የሁሉም ኮሌጆች ተማሪዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች አስተያየቶችን፣ ጥቆማዎችንና ጥያቄዎችን በመሰንዘር የመብራት፣ የኢንተርኔት፣ የውሃና ሌሎች ተያያዥ አገልግሎቶች አካባቢ የሚታዩትን ክፍተቶችና ከፍተኛ መሻሻሎች ገምግመዋል፡፡

ዲኖቹ ለአስተያየትና ጥቆማ ሰጪዎች ምስጋና በመቸር ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በሠጡበት ወቅት የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል መምህራን የትምህርት ክፍለ ጊዜዎችን በአግባቡ እንዲጠቀሙ መደረጉን፣ የብቃት ችግር አለባቸው የተባሉ የአንዳንድ የውጭ አገር መምህራን ኮንትራት መቋረጡን እንዲሁም መምህራን የተማሪዎችን ፈተና በወቅቱ አርመው ውጤታቸውን የሚያሳዩበት ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ከትምህርት ክፍሎች ጋር በመተባበር እየተሠራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ የ1 ለ 5 አደረጃጀት በሁሉም ክፍሎች ውጤታማ ሥራ እንዲያከናውን የሚያስችልና ክትትል የሚያደርግ ከአስተዳደር ሰራተኞች፣ ከመምህራንና ከተማሪዎች የተወከለ የሱፐርቪዢን ቡድን ተቋቁሞ ሥራ ላይ መሆኑንም አሳውቀዋል፡፡

የሁሉም ኮሌጆች ዲኖች እንደተናገሩት ከተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ከአስተዳደር ሠራተኞች የስኬት ማነቆ ሆነው የተለዩትን ችግሮች ለመቅረፍ በተቀመጠው መርሃ ግብር መሠረት እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀው በቀጣይ በመካከለኛና በረዥም ጊዜ ሊፈቱ የታቀዱ ችግሮችን በተቀናጀ ጥረት ለመሻገር በርትተው እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል፡፡

ዶ/ር ፈለቀ ኮንፈረንሱን ሲያጠቃልሉ በመካከለኛና በረዥም ጊዜ ሊተገበሩ የታቀዱ እንዲሁም እስከአሁን መፍትሔ ያልተሰጣቸው የተወሰኑ የአጭር ጊዜ ተግባራት በቀጣይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራባቸው በመግለጽ የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ የትምህርት ልማት ሠራዊት ግንባታን ይበልጥ በማጠናከር የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ሁሉም ባለድርሻዎች በቅንጅት እንዲሠሩ አሳስበዋል፡፡

  1. የግብርና ሣይንስ ኮሌጅ ዘርፈ ብዙ ምርምሮችን እያከናወነ መሆኑ ተገለፀ
  2. የተማሪዎች ኅብረት ለአረጋዊያንና ወላጅ አጥ ሕፃናት የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ የምሳ ግብዣ አደረገ፡፡
  3. ሰላም ፎረም ለአባላትና ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡
  4. የኮምፒዉተር ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የአይ ሲ ቲ አዉደ-ርዕይ አቀረቡ፡፡

Page 450 of 513

  • 445
  • 446
  • 447
  • 448
  • 449
  • 450
  • 451
  • 452
  • 453
  • 454

Downloads

  • Newsletter
  • Registrar
  • Academic Calendar
  • Finance & Budget Transparency

Quick Links

  • News
  • Vacancies
  • AMU Intranet
  • ICT Center

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • Facebook
  • X
  • Telegram
  • Youtube
  • Email

Contact us

Corporate Communication
P.O. Box 21
Arba Minch University

Tel: +251-46881-4986
Fax: +251-46881-0820/0279
E-mail: corcom@amu.edu.et , ictc@amu.edu.et

Registrar

  • About Us
  • Alumni
  • Alumni Registration
  • Contact us

Colleges

  • Agriculture
  • Business & Economics
  • Medicine and Health Sciences
  • Natural Sciences
  • Social Sciences & Humanities

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning

Copyright © 2024 Arba Minch University. Built by Meftihe.

  • Campus Guide
  • Contact Us
  • Sitemap