• SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • AMU
    • About AMU
    • Presidents Message
    • Campus Guide
    • Contact us
  • Administration
    • Presidents' Office
      • AMU President
      • Academic Affairs
      • Research and Community Service
      • Administration
  • Directorates
  • Academics
    • School of Graduate Studies
    • Institutes
      • Arba Minch Institute of Technology
      • Arba Minch Water Technology
    • Colleges
      • Agriculture
      • Business & Economics
      • Medicine and Health Sciences
      • Natural & Computational Sciences
      • Social Sciences & Humanities
      • Continuing & Distance Education
      • Sawla Campus
    • Schools
      • School of Law
      • School of Pedagogical and Behavioral Sciences
      • School of Medicine
    • Sport Academy
  • Research
  • Registrar
    • About Us
    • Alumni Registration
    • Alumni
  • Partnership
    • Our Partners
      • International Partners
      • Local Partners
    • Ongoing Projects
    • Completed Projectss
      • Recently Completed
      • Past Projects
    • GCPM Online Forms
  • Journals
    • OMOIJS Journal
    • EJBSS Journal
    • EJWST Journal
    • AMUJCLS Journal
    • EIJET journal
  • Symposia
    • Enset Symposium
    • Enset Symposium 2024

የሙስና ወንጀልን አስመልክቶ ለተመራቂ ተማሪዎች ሥልጠና ተሰጠ ፡፡

Details
Sun, 29 March 2015 9:00 pm

የፌዴራል የስነ -ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአምስቱም ግቢዎች ለሚገኙ ተመራቂ ተማሪዎች ከመጋቢት 21 -25 /2007ዓ/ም ድረስ በሙስና ፅንሰ-ሃሳብ ፣ በስነ-ምግባርና በሙስና ወንጀል ህጎች ላይ ያተኮረ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የሥልጠናው ዓላማ ተማሪዎቹ ተመርቀው ወደስራ ዓለም በሚቀላቀሉበት ወቅት የተለያዩ ብልሹ አሠራሮች ሊያጋጥሟቸው ስለሚችሉ ከወዲሁ ግንዛቤ ኖሯቸው ራሳቸውን በስነ-ምግባር በማነፅና ሙስናን በመከላከል የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ለማስቻል እንደሆነ የኮሚሽኑ ከፍተኛ አማካሪ አቶ ሙሉነህ ጉግሳ ገልፀዋል ፡፡

ከኮሚሽኑ የመጡት አቶ ሃረጎት አብረሃም የሙስና ወንጀል ምንነትን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፡-ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት ፣ በሌላ ሰው መብት ላይ ጉዳት እንዲደርስ በማሰብ ለመንግስት ሰራተኛ የማይገባ ጥቅም ለመስጠት ቃል የገባ፣ የሰጠ፣ ያቀረበ ወይም ለማቅረብ የተስማማ እንዲሁም በአግባቡ ለተፈፀመ ወይም በአግባቡ ወደፊት ለሚፈፀም የመንግስት ስራ የማይገባ ጥቅምን የሰጠና መሰል ተግባራትን ያከናወነ የሙስና ወንጀል እንደፈፀመ የሚቆጠር መሆኑን አብራርተዋል ፡፡

በተጨማሪም በስልጣን ያለ አግባብ መገልገል፣ የመንግስት ስራን በማያመች መንገድ መምራት ፣በአደራ የተሰጠን ዕቃ ለሌላ ማዘዝ፣በህገ ወጥ መንገድ ገንዘብ መሰብሰብ ፣ ያለአግባብ ጉዳይን ማጓተት፣ ዋጋ ያለውን ነገር ያለ በቂ ክፍያ ማግኘት፣ ያለአግባብ ፈቃድ መስጠትና ማፅደቅ እንዲሁም ምንጩ ያልታወቀ ንብረትና ገንዘብ መያዝ የመሳሰሉት በመንግሥት ሠራተኞች የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች መሆናቸውን ጠቁመው ተመራቂ ተማሪዎች በቀጣይ ወደ ስራ አለም ሲገቡ ለሙስና ወንጀል እንዳይጋለጡ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል ፡፡

ሠልጣኞቹ በሰጡት አስተያየት ጊዜን በአግባቡ አለመጠቀም ፣ስራ ገበታ ላይ በሰዓት ያለመገኘትና ተገቢውን አገልግሎት አለመስጠት፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ የሆነ አካሄድ ያለመኖሩ በራሱ ሙስና መሆኑን ተናግረው ስልጠናው በዚህ ሰዓት መሰጠቱ የሙስና ወንጀሎችን ለይተን እንድናውቅና ቅድመ ጥንቃቄ እንድናደርግ የሚያስችለን ነው ብለዋል ፡፡

Self-belief, positive energy make the way, says Mikias

Details
Mon, 23 March 2015 1:23 pm

You just can’t ignore Mikias Solomon Assefa because of his ordinary look; glint in his eyes and flailing ambition would make you go deeper into his persona. He isn’t tall neither cute, but his achievement is extraordinary!

Read more: Self-belief, positive energy make the way, says Mikias

Graduation: Work for nation’s sustainable growth, says Dr Feleke

Details
Mon, 23 March 2015 8:36 am

‘‘This graduation is special for the first batch of 35 Graduates of Medical Science from College of Medicine and Health Sciences because today AMU is also laying the foundation stone for 300-bedded Referral-cum-Teaching hospital in Arba Minch, said University President, Dr Feleke Woldeyes. Click here to see the Pictures.

Read more: Graduation: Work for nation’s sustainable growth, says Dr Feleke

Painting Expo: Sinafikish talks peace, unity; instills hope

Details
Mon, 23 March 2015 8:03 am

Ethiopian contemporary artist Sinafikish Zeleke’s 20 acrylic paintings on display at PG Building Library Hall, Main Campus are optimistic canvas showcasing Ethiopian ethos, cultural spender, social mores and ongoing transition from under-development to self-sufficiency. Click here to view the Pictures.

Read more: Painting Expo: Sinafikish talks peace, unity; instills hope

አለም አቀፍ የሚቲዎሮሎጂ ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ ፡፡

Details
Sun, 22 March 2015 9:00 pm

የአለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት / wmo/ ከተቋቋመበት እ.ኤ.አ ከ19 50 ዎቹ ጀምሮ አለም አቀፍ የሚቲዮሮሎጂ ቀን በየዓመቱ መጋቢት 14 / March 23 /የሚከበር ሲሆን በዚህ ዓመት “Climate knowledge for climate action” በሚል መሪ ቃል በአ/ም/ዩ በተፈጥሮ ሣይንስ ኮሌጅ በፓናል ውይይትና በችግኝ ተከላ ተከብሯል ፡፡

የሚቲዎሮሎጂ ቀን ተማሪዎችና መምህራን የወቅቱን የአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም የባህር ነውጦችን መንስኤ በማጥናት በተለይ አርሶ አደሩ በቂ ድጋፍና ግንዛቤ የሚያገኝበትን መንገድ ለማመቻቸት ግኝታቸውን የሚያስተላልፉበት አጋጣሚ መሆን እንዳለበት የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አጌና አንጁሎ ተናግረዋል ፡፡

የበዓሉ ዋነኛ ዓላማ በሰው ልጆች የእለት ከእለት እንቅስቃሴ የሚፈጠረውን የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከልና ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን ለመቀነስ የሚያስችሉ ግንዛቤዎችን ለማሳደግ ከሳይንሱ ጋር የተያያዙ መረጃዎችንና እውነታዎችን ማስጨበጥ እንደሆነም የሚቲዎሮሎጂና ሃይድሮሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ መ/ር ሙሉጌታ ገናኑ ገልፀዋል ፡በተጨማሪም መምህሩ በሚቲዎሮሎጂ ትምህርት ክፍል እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በዝርዝር አቅርበዋል ፡፡

የሚትዎሮሎጂ ትምህርት ከሁሉም የሳይንስ ትምህርቶች ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያለው ዓለም አቀፋዊ ሳይንስ እንደመሆኑ መጠን በጤና ፣በአካባቢ ጥበቃ ፣በንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ የትምህርት ክፍል ነው፡፡ የኮሌጁ ዲን ዶ/ር አለማየሁ ኃ/ሚካኤል ፕሮግራሙን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት በዕለቱ የተነሱት ጉዳዮች የሰዎችን ግንዛቤ ከማስፋት አንፃር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸውና አስተማሪ መሆናቸውን በመግለፅ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ከሚደረጉ ጥናትና ምርምር ስራዎች ጎን ለጎን ኮሌጁ በእለቱ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ኃላፊነት እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡

 

ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

አ/ም/ዩ

  1. Ethiopian female artist Senafikesh’s art expo begins on 17th
  2. AMU to lay foundation stone for Hospital; host graduation ceremony
  3. IoT to launch MSc in Irrigation Engineering and Management in Oct 2015
  4. ESSS Arba Minch branch gets 4 telescopes; managing panel formed

Page 467 of 523

  • 462
  • 463
  • 464
  • 465
  • 466
  • 467
  • 468
  • 469
  • 470
  • 471

Downloads

  • Newsletter
  • Registrar
  • Academic Calendar
  • Finance & Budget Transparency

Quick Links

  • News
  • Vacancies
  • AMU Intranet
  • ICT Center

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • Facebook
  • X
  • Telegram
  • Youtube
  • Email

Contact us

Corporate Communication
P.O. Box 21
Arba Minch University

Tel: +251-46881-4986
Fax: +251-46881-0820/0279
E-mail: corcom@amu.edu.et , ictc@amu.edu.et

Registrar

  • About Us
  • Alumni
  • Alumni Registration
  • Contact us

Colleges

  • Agriculture
  • Business & Economics
  • Medicine and Health Sciences
  • Natural Sciences
  • Social Sciences & Humanities

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning

Copyright © 2025 Arba Minch University. 

  • Campus Guide
  • Contact Us
  • Sitemap