• SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • AMU
    • About AMU
    • Presidents Message
    • Campus Guide
    • Contact us
  • Administration
    • Presidents' Office
      • AMU President
      • Academic Affairs
      • Research and Community Service
      • Administration
  • Directorates
  • Academics
    • School of Graduate Studies
    • Institutes
      • Arba Minch Institute of Technology
      • Arba Minch Water Technology
    • Colleges
      • Agriculture
      • Business & Economics
      • Medicine and Health Sciences
      • Natural & Computational Sciences
      • Social Sciences & Humanities
      • Continuing & Distance Education
      • Sawla Campus
    • Schools
      • School of Law
      • School of Pedagogical and Behavioral Sciences
      • School of Medicine
    • Sport Academy
  • Research
  • Registrar
    • About Us
    • Alumni Registration
    • Alumni
  • Partnership
    • Our Partners
      • International Partners
      • Local Partners
    • Ongoing Projects
    • Completed Projectss
      • Recently Completed
      • Past Projects
    • GCPM Online Forms
  • Journals
    • OMOIJS Journal
    • EJBSS Journal
    • EJWST Journal
    • AMUJCLS Journal
    • EIJET journal
  • Symposia
    • Enset Symposium
    • Enset Symposium 2024

የኮምፒዉተር ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የአይ ሲ ቲ አዉደ-ርዕይ አቀረቡ፡፡

Details
Thu, 23 July 2015 11:01 am

በኮምፒዉተር ሳይንስ ትምህርት ክፍል ከ1-4ኛ አመት ድረስ በሚማሩ ተማሪዎች የተሰሩ 16 አዳዲስ የኮምፒዉተር ፕሮግራሞች በዋናዉ ግቢ እና በአባያ ግቢ ከግንቦት 11-12/2007 ዓ.ም ድረስ ለዕይታ ቀርበዋል፡፡

በዓውደ ርዕዩ ለዕይታ ከቀረቡ የኮምፒዉተር ፕሮግራሞች መካከል የዉጪ ሀገርና የሀገር ዉስጥ ጎቢኚዎች ባሉበት ሆነዉ በኢንተርኔት አማካኝነት ሆቴል ለመያዝ፣የአዉቶብስ ቲኬት ለመቁረጥ ፣ ስለቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎች መረጃ ለማግኘት የሚያስችላቸዉና በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በተማሪዎች መመረቂያ ጽሁፎች ዝግጅት ወቅት የሚከሰቱ ኩረጃዎችን ለመቆጣጠር የሚያግዙ ፕሮግራሞች ተጠቃሾች ናቸዉ፡፡

የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ኤግዚብሽኑን በጎበኙበት ወቅት እንደተናገሩት በኤግዚብሽኑ የቀረቡት የኮምፒዉተር ፕሮግራሞች ችግር ፈቺ ከመሆናቸዉ በተጨማሪ በተማሪዎች የግል ጥረት መሰራታቸዉ የሚበረታታ ነዉ፡፡ ዶ/ር ፈለቀ አክለዉ ተማሪዎች እንዲህ አይነት ሥራ መስራታቸዉ ከበስተጀርባቸዉ ጠንካራ መምህራን መኖራቸዉንና የዩኒቨርሲቲዉን የትምህርት አሰጣጥ ጥራት የሚያሳይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ በበኩላቸዉ በኤግዚብሽኑ የቀረቡት የፈጠራ ሥራዎች ዓለም በኮምፒዉተር ዕዉቀት የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ ከምናከናዉናቸዉ ተግባራት አንዱ አካል መሆኑን ጠቅሰዉ የፈጠራ ሥራዎቹ ወደ ተግባር ሊለወጡ የሚችሉ ናቸዉ ብለዋል፡፡

በአዉደ ርዕዩ ወቅት በተሳታፊዎች በተሰጠዉ ድምጽ አሸናፊ የሆነዉ በተማሪዎች መመረቂያ ጽሁፎች ዝግጅት ወቅት የሚከሰቱ ኩረጃዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችል ፕሮግራም በመስራት ለዕይታ ያቀረበዉ-የ4ኛ አመት ተመራቂ ተማሪ አቤል ተመስገን ነዉ፡፡ተማሪ አቤል እነደተናገረዉ ተመራቂ ተማሪዎች መመረቂያ ጽሁፎቻቸዉን በሚያቀርቡበት ወቅት በፊት የተመረቁ ተማሪዎች ከሰሯቸዉ ሥራዎች በተወሰነ መልኩ ኮርጀዉ ስለሚያቀርቡ በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተማሪዎች የተሰሩ ፕሮጀክቶች አንዳንዶቹ ተመሳሳይነት ይታይባቸዋል፡፡ ስለዚህ እሱ የሰራዉ የኮምፒዉተር ፕሮግራም በኢኒስቲትዩቱ የተሰሩ ፕሮጀክቶችን በጠቅላላ መዝግቦ መያዝ ስለሚያስችል ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ሲመጡ በቀላሉ ለይቶ ያሳዉቃል፡፡ኩረጃ በአንድ የኒቨርሲቲ ብቻ የማይወሰን አለም አቀፋዊ እና ሀገር አቀፋዊ ባህሪ ስላለዉ አሁን የሰራዉን ፕሮጀክት በዚህ ደረጃ የማሳደግ ህልም እንዳለዉም ተማሪ አቤል አስምሮበታል፡፡

በአዉደ ርዕዩ መዝጊያ ስነ-ስርአት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲዉ መምህራን፣ተማሪዎች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በሰጡት አስተያየት እንዲህ አይነት አዉደ ርዕይ መካሄዱ ሌሎችንም ተማሪዎች የሚያነሳሳ መሆኑን በመጥቀስ የአዉደርዕዩ አቅራቢ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን ትምህርት በተግባር አሳይተዋል ብለዋል፡፡



24ኛው የግንቦት 20 የድል በዓል በዋናው ግቢ በድምቀት ተከበረ

Details
Thu, 23 July 2015 11:00 am

የግንቦት 20 ሃያ አራተኛ አመት የድል በዓል በዋናው ግቢ ግንቦት 26/2007 ዓ.ም ‟ከብተና ስጋት ወደ ለዉጥ አብነት የተሸጋገረች ሀገር - ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በድምቀት ተከበረ፡፡

የኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍስሃ በቀለ የግንቦት 20 ፍሬዎችን በተመለከተ ዘርዘር ያለና ሁሉንም ዘርፎች የዳሰሰ የመወያያ ሰነድ ለታዳሚዎች አቅርበዉ ጠለቅ ያለ ዉይይት ተደርጎበታል፡፡በሰነዱ ከግንቦት 20 ድል በኋላ በሀገራችን በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ ፣በመሰረተ ልማት ፣ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እና በሰላምና የውጭ ግንኙነት ዘርፎች የተመዘገቡ ድሎች ተዳስሰዋል፡፡

ሰነዱን መሰረት በማድረግ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከግንቦት 20 ድል ወዲህ በሀገሪቱ የብሄር፣ የቋንቋ ፣ የባህል፣ የጾታ እና የሃይማኖት ነፃነቶች የተከበሩ ሲሆን በኢኮኖሚ ዕድገት ረገድም አለም ባንክና ሌሎች አለም-አቀፋዊ ተቋማት የመሰከሩለት እድገት የተመዘገበ መሆኑን ጠቅሰዉ እኛም የአይን እማኞች ነን ብለዋል፡፡በተለይም በትምህርትና በጤና ተቋማት ግንባታና ተደራሽነት እንዲሁም በመንገድ ግንባታ፣በቴሌኮሙኒኬሽንና በመብራት ኃይል አቅርቦት የተመዘገቡ ለዉጦች ለሌሎች ሀገራትም ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም አስተያየት ሰጪዎች የተጀመረዉን የህዳሴ ጉዞ ማስቀጠል የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በበአሉ አከባበር ስነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ እንደገለፁት ግንቦት 20 ለመላዉ ኢትዮጵያዊያን አንድ የጨለማ ምዕራፍ ተዘግቶ ሌላ አዲስ ብርሃን ፈንጣቂ ምዕራፍ የተጀመረበት ነዉ፡፡በመሆኑም የሀገራችን ህዝቦች በሽምቅ ውጊያ፣በግድያ፣በአፈናና ዉምብድና ከመሰቃየት ወጥተዉ ወደ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ ተሸጋግረዋል፡፡

የጋሞ ጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸዉ የትግሉ ሰማዕታት የህዝብን አጀንዳ አንግበው ወደ ትግሉ ሲገቡ ለራሳቸው እንደማያልፍላቸውና የህይወት መስዋዕትነት ሊከፍሉ እንደሚችሉ ቢያውቁም ለመጪው ትውልድ ብርሃንን ይፈነጥቁ ዘንድ ተሰውተዋል ብለዋል፡፡ በመሆኑም የዛሬዉ ትዉልድ የህዳሴ ጎዳና ላይ ያለች ሰላማዊ ሀገር በመረከቡ ዕድለኛ ስለሆነ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ሁሉ በአግባቡ በመወጣት ሀገራችን እየተገበረች ለምትገኘዉ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ጉዞ የጀርባ አጥንት መሆን አለበት ሲሉም ተደምጠዋል፡፡በመጨረሻም የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሀገራችን ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ የምታደርገዉን ሽግግር በመማር-ማስተማር፣በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ከወትሮዉ በበለጠ እንዲደግፍ አሳስበዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲዉ ከፍተኛ አመራሮች፣የአስተዳደርና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች፣መምህራንና ተማሪዎች በበአሉ ላይ የተገኙ ሲሆን የጋሞ ጎፋ ዞን ባህላዊ ኪነት ባንድ የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን በማሰማት በአሉን አድምቋል፡፡

Guidance, hard works and determination is the key: AMU topper

Details
Wed, 01 July 2015 7:08 am

This year’s overall topper of Arba Minch University, Tarekegn Tumebo Kariba, is a humble son of a farmer; he is from Kambata Tembaro zone. He has encountered difficulties but didn’t give in on the contrary come out successful.

Read more: Guidance, hard works and determination is the key: AMU topper

INSTITUTE AND COLLEGE-WISE LIST OF TOP-SCORING STUDENTS

Details
Wed, 01 July 2015 6:47 am

List of top scoring students :-

Read more: INSTITUTE AND COLLEGE-WISE LIST OF TOP-SCORING STUDENTS

28th Convocation: Contribute in nation building, graduates told

Details
Wed, 01 July 2015 6:31 am

Arba Minch University’s 28th Convocation conducted in the tastefully decorated Auditorium at Abaya Campus on 27th June 2015, has many firsts. Of this year’s 4400 graduates, 4287 were under and 113 post-graduates from 36 different streams. Of total pass-outs, 65% alone were from engineering streams while remaining 35% constituted other subjects.Click here to see the Pictures.

Read more: 28th Convocation: Contribute in nation building, graduates told

  1. Live Graduation Ceremony via YouTube, Digital Signage screens
  2. Science, the way out for present global problems: Researchers
  3. Mirab Abaya: AMU signs Pact with Gamo Gofa Zone Agri Office
  4. College of Continuing and Distance Education's Summer program notice

Page 462 of 523

  • 457
  • 458
  • 459
  • 460
  • 461
  • 462
  • 463
  • 464
  • 465
  • 466

Downloads

  • Newsletter
  • Registrar
  • Academic Calendar
  • Finance & Budget Transparency

Quick Links

  • News
  • Vacancies
  • AMU Intranet
  • ICT Center

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • Facebook
  • X
  • Telegram
  • Youtube
  • Email

Contact us

Corporate Communication
P.O. Box 21
Arba Minch University

Tel: +251-46881-4986
Fax: +251-46881-0820/0279
E-mail: corcom@amu.edu.et , ictc@amu.edu.et

Registrar

  • About Us
  • Alumni
  • Alumni Registration
  • Contact us

Colleges

  • Agriculture
  • Business & Economics
  • Medicine and Health Sciences
  • Natural Sciences
  • Social Sciences & Humanities

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning

Copyright © 2025 Arba Minch University. 

  • Campus Guide
  • Contact Us
  • Sitemap